2013 ዲሴምበር 27, ዓርብ

Henok Stotaw ኄኖክ ስጦታው poem Tegelebetu



http://etopics.weebly.com/

የተለያዩ የጽሁፍ ስራዎች በድምጽ የሚተረኩበት የበየነ መረብ አገልግሎት ነው፡፡በየሳምንቱ አርብ ረፋድ ላይ በፌስ ቡክ ገጽ ላይ በጥራት ይሰማል፡፡ልክ የዛሬ ወር ስራውን ሲጀምር በመጀመሪያ ያስድመጠው ስራ የኄኖክ ስጦታው "ተገለበጡ" ግጥምን ነበር፡፡

አዘጋጅ፡- በሸገር ሼልፍ ፕሮግራም እና በ17 መድፌና ሃያ ምናምን ቁምጣ መጽሐፉ የሚታቀው ሃብታሙ ስዩም ነው፡፡

2013 ኖቬምበር 12, ማክሰኞ

“ሀ-አይሞትም “ለ”ም ገና ይወለዳል! -- ቱዋ (ጋርጋንቱዋ)


“ሀ-አይሞትም “ለ”ም ገና ይወለዳል!

Written by ቱዋ (ጋርጋንቱዋ)

አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ጥቅምት 30 ቀን 2006ዓ.ም

ጥበብ ለሁሉም ሰው ትገባለች ወይንም ትገባለች (“ገ” ይጠብቃል)? የሚለው ጥያቄ ሰርክ ያጭበረብረኛል። ነገር ግን ድርጊታችን ጥያቄውን መልሶልኝ አገኝና ወደ ተጨባጩ እውነታ አመዝናለሁ፡፡ በተጨባጩ እውነታ ላይ፣ ድርጊታችን እንደሚያሳየኝ፤ ጥበብ ብለን የምንጠራቸውን የፈጠራ ውጤቶች የምናቀርበው ለብዙሀኑ ማህበረሰብ ነው፡፡ ስለዚህም ቢገባቸው ነው የተገባችው እልና ጭጭ እላለሁ፡፡ ሳይገባኝ የተገባኝ አንድ የግጥም መጽሐፍ እጄ ገባ። ገጣሚው ሄኖክ ስጦታው ነው፡፡ የመጽሐፉ አርዕስት “ሀ-ሞት” የተሰኘ ነው፡፡ መጀመሪያ በችኮላ ሳገላብጠው ብዙም አልመሰጠኝም፡፡ እንደ ሌላው መጽሐፍ ማከማቻው ላይ ጣል አደረኩት፡፡ ጠብ በማይሉ ግጥሞች ለብዙ አመታት ተንገላትቻለሁ፡፡ ትንሽ ቀናት አለፉ፡፡

ሌላ ሰው መጽሐፉ ጥሩ መሆኑን ለማስረገጥ እየመረጠ ያነብልኝ ጀመረ። መጽሐፉ ያው ሆኖ ሳለ…አንዴ ሳይጥመኝ በኋላ መልሶ ለምን እንደጣመኝ ለማወቅ በመፈለጌ ወደ ማሰላሰል ገባሁኝ፡፡ ማርሴል ፕሮስት የግጥምን ምንነት “The superimposition of two systems: thought and meter” ብሎ ይገልፀዋል፡፡ ምጣኔ/ምት/ ዜማ እና ሃሳብ አብረው እንዲስማሙ የተገደዱበት ልዕለ ህግ ነው እንደማለት፡፡ በምጣኔ እና ምት ዜማ መፍጠራቸው የተፈጥሮ ጉዳይ ነው፡፡ በግጥም ቤት መድፋት ወይንም መምታት ለጥበብ ብለን የምናደርገው ሳይሆን ለተፈጥሮአችን እውነት ስለሆነ የምንከተለው፣ ሳንመርጥ የተገደድንበት ነገር ነው። ግዴታችንን መወጣታችን ነው ውበቱ፡፡ ጤነኛ መሆናችንንም ገላጭ ነው። Superimpositio n የተባለውም በዚሁ የተፈጥሮ ግዴታችን ምክንያት ነው፡፡ ከምጣኔው፣ ከምቱ እና ከዜማው በኋላ ግን የሰው ግዛት ይጀምራል፡፡ በዜማው፣ በምቱ እና በምጣኔው ውስጥ ለማወቅ የምንሞክረው ሃሳብ ( ጭብጥ) ግን ከሰው ልጅ የነፃነት ምርጫ (volition)  የመጣ ነው፡፡

ያለ ሃሳብ እና ሃሳብ የሚፈጥረው ትርጉም በዜማ እና በምት ብቻ የሚመጣ ጭብጥ የለም። ጭብጥ ከሌለ “እና ምን ይጠበስ?!” የሚለው ጥያቄ ይመጣል። የሁለቱ የግዴታ ጥምረት ውጤት ትርጉም ያለው ውበት፣ እውነት…እና ጥበብ ይሆናል። ቅድሚያ ለቅርጽ መገዛት ወይንም በመጀመሪያ “ሃሳቡ ይቀድማል” ማለት፤ ሁለቱን ከመጣመር አያግዳቸውም፡፡ ከታገዱም ውበት አይሆኑም፡፡ መጀመሪያ ለሴት መብት መታገል ዞሮ - ዞሮ ወንዱን መግደል እስካልሆነ ድረስ ነው እድገት የሚሆነው እንደማለት፡፡ ጥበብም ይሄንኑ መሰረት የሚከተል የጥምረት ህግ ነው፡፡ ነገር ግን፤ እኔ ዛሬ መግለጽ የፈለኩት “ግጥም ማለት ምንድነው? የሚለውን ጥያቄ አይደለም። ትርጉምን ሳናውቅ ግጥም ግን ይሰማናል፡፡ ሰው እስከሆንን ድረስ ትርጉሙን ባናውቅም ቅኔ መፍጠር እንችላለን። የግጥሙን ትርጉም እንጂ የግጥምን ትርጉም የማወቅ ግዴታ አልተጣለብንም፡፡ አሁን ወደ ዋናው አጀንዳዬ ልመለስ፡፡ ግጥም እንዲነበብ እና እንዲወደድ ማንበብ መቻል እና የሚነበበው ነገር የሚወደድ ተደርጎ መፃፉ ብቻ እንደማይበቃ የተረዳሁት በ”ሀ-ሞት” የግጥም መድበል ነው ብያለሁ፡፡

ገጣሚው ነዋሪነቱን ተጠቅሞ ያበረከተው የጥበብ ስራው ከእኔ ነፃነት እና ምርጫ ጋር የሚገናኘው እንዴት ነው?... በሚል ጥያቄ የተጭበረበረብኝን (መጽሐፉን መጀመሪያ ለብቻዬ አለመረዳት በኋላ በሰው ምርጫ ጥቆማ አማካኝነት መልሶ መረዳት)…ለማስተካከል ተነሣሁ፡፡ ምናልባት በመጀመሪያ ራሴ መጽሐፉን ሳገላብጥ ባገኘሁዋቸው ግጥሞች ምክንያት ሊሆን ይችላል እንደ መናቅ ብዬ የተውኩት፡፡ በብዙ አሰልቺ ግጥም እና አቀራረብ የተጉላላ ሰው፣ በሰለቸ አይኑ ስለሆነ አዲሱንም የሚመለከተው ሊጭበረበር ይችላል፡፡ ለምሳሌ “በግ ሳር እና በግ” የሚለው ግጥሙ፡፡ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ይሆነኛል፡፡ በፊት…/በግ ነበርን/ሣር ቅጠሉን እየቃረምን፡፡/አሁን/ሣር ሆነናል/ በጐች ይታዩናል፡፡ ግጥሙ ምንም የሚወጣለት ነገር የለም፡፡ የተለመደ ከመምሰሉ በስተቀር፡፡ በ90 ዎቹ አጋማሽ አካባቢ “ድሮ አህያ እንዳልነበርክ በጅቦቹ መሀል አህያ ሲበዛ ዛሬ ጅብ ሆነሀል” አይነት የበዕውቀቱ እና የኑረዲን ኢሣ የሃሳብ ጥምዞች ጋር የተወራረሰ ስለመሰለኝ …”ጥሩ ሲደጋገም ይሰለቻል” ብዬ ሊሆን ይችላል፤ መጀመሪያ ችላ ያልኩት፡፡

በእርግቦች መሀል/እርግብ ተመስላ /”እርግብናት”/ያልናቱ/ላባ ተከልላ/ ስትከፍተው አፏን/አየን ጥርስ አብቅላ/ ይሄም ከሚሊኒየሙ በፊት የተፃፉ ወይንም የታሰቡ ግጥሞች የሃሳብ አጠቃለል እና “ለካ” የሚለውን ድሮ ከሚታሰበው የተቃረነ፣ ያፈነገጠ… የፍለጋ ጭብጥ የሚቋጠርበትን የዘመን መንፈስ የሚያስታውሰኝ በመሆኑ ሊሆን ይችላል …መጀመሪያ መጽሐፉ አይገባኝም (ገ ይጠብቃል) ያልኩት፡፡ አመተ ምህረቶቹን ከግጥሞቹ አስቀድሜ ብመለከት ኖሮ ግን፤ ተመስጦ ላገኝ የምችለው፤ ወይንም ተመስጦን የሚሰጠኝ ያልተደጋገመው፣ አዲሱ (ኦሪጅናሉ) በመሆኑ፤ ትላንትን ሳይሆን ዛሬን የሆኑት ላይ እንደሚገኙ መጠርጠር ነበረብኝ፡፡ እንደእኔ ዛሬ የሚገኘው የሚሊኒየሙን ወንዝ ከተሻገርን…የአምስት አመት የእድገት እና የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማስፈፀም መንፈራገጥ ከጀመርን በኋላ ያሉት አመታት ሂደት ውስጥ ነው፡፡ …የኑሮ ውድነቱም፣ የልማታዊ መንፈራገጦችም፣ የነፃነት አፈናዎችም…የነዋይ ፍቅር እና የፎቅ ፎንቃ…እና የተለያዩ እጥረቶች (በውጥረት መልክ) የተከሰቱብን በእነዚህ አምስት ዓመታት ሂደት ነው፡፡ ከሄኖክ ግጥሞች ውስጥ ማተኮር የነበረብኝ ገጣሚው በዚህ ሂደት ሳለ የፃፋቸው ላይ መሆን ነበረበት፤ ግን ይሄን መጀመርያ ላይ ማድረግ አልቻልኩም፡፡

ለስህተቴ ራሴን ይቅርታ እላለሁ! በነፃነት አንድን አዲስ ስራ ለመመልከት፤ አይን እና መስተሀልይ ብቻ በቂ አይደሉም፡፡ ነፃነት በመሰልቸት እና ለአመታት በተደጋገሙ አታካቾች የፈጠራ ተብዬ ውርጅብኝ…አይንም በፍዘት አይን ሞራ ይጋረዳል፡፡ መስተሀልይም ሁሉንም ነገር እንደ አዲስ የመመርመር (የህፃን ልጅ የየዋህነት) ቅልጥፍናውን ያጣል፡፡ የሄኖክ ስጦታው “ሀ-ሞት” የግጥም መድበልን በአዲስ እይታ ለማየት የሌላ ሰው እርዳታ አስፈልጐኝ ነበር። የሚረዳኝ በማግኘቴ ላየው ቻልኩ፡፡ በ2004  ዓ.ም የፃፈው “የቱባ ክር ጫፎች” ይኼንኑ የእኔን መሰል ችግር በግዝፈት ኢትዮጵያን አሳክሎ ያቀረበበት ነው፡፡ “የለውም ጫፍ ብሎ ቆርጦ የሚጀምር አራት ጫፍ ያገኛል፣ ክሩን ሲተረትር/ጫፍ መያዝ በጥጦ፤ በጥሶ መቋጠር/ኢትዮጵያን አድርጓታል የብዙ ጫፍ ሀገር/ሞልቷታል እያዬ አያልቅም ቢቆጠር/አያሌ ጫፍ ወራጅ፣ ዕልፍ ቆርጦ ጀምር/ተብትቦ የሚተው ደህነኛውን ድውር/ለመፍታት ሲነሳ ጠቅሎ የማይጀምር” ምናልባት ደረጀ በላይነህ በአለፈው አመት (ይመስለኛል) ባቀረበው አንድ መጣጥፍ፤ ግጥም ሞቷል የተባለው ውሸት መሆኑን፤ የሞተው አዲስ ባለመውለዱ ቢሆንም… የተረገዙ እና ቀን እየገፉ የመጡ መኖራቸውን ነግሮን ነበር፡፡

እኔም በዚህ የሄኖክ መጽሐፍ ይሄንኑ ብያኔውን ተቀብያለሁ፡፡ ማለት የሚፈልገውን ማለት መቻል ራሱ የህያውነት ምስክር ነው፡፡ የበረከት በላይነህን “የመንፈስ ከፍታ” ይዘን የሄኖክን “ነፃነት” ብናክልበት ከፍዘታችን መንቃታችን እርግጥ ይሆናል፡፡ “የቆጥ ላይ ቅስቀሳ ፩” የሚለው ግጥም ቀስቃሽ የሚፈልግ እንቅልፋምን ሳይሆን ቀስቃሽ የማይፈልግ አንቂን የሚዘክር ነው፡፡ ምናልባት ሳይቀሰቀስ ለመንቃት የቻለው ራሱ ገጣሚው ሊሆን ይችላል። ቀድሞ የነቃ፤ ቀስቃሽ እንጂ ተቀስቃሽ ሊሆን አይችልም፡፡ የገጣሚውን መንቃት ከራሱ በስተቀር እማኝ ሊሆን የሚችል ባይኖርም፤ በግጥሙ አማካኝነት ግን የሱን መንቃት እና የኛን መተኛት እንገነዘባለን። የተኙት ቀስቃሾች የነቁትን ሲቀሰቅሱ:- “ነግቷል! ነግቷል! ነግቷል! /ይሉናል/ይሉናል/ይወተውተናል/ተነሱ ተነሱ ተነሱ/ይጮኻሉ እነሱ/እየቀሰቀሱ…፡፡/ተቀስቅሰን በጩኸቱ/ተበስሮልን መንጋቱ፤/አደባባይ ስንወጣ/ቀስቃሻችን ከየት ይምጣ” ሄኖክ እና “ሀ-ሞት” እኔን የቀሰቀሱኝ ወደ አንድ መልዕክት ነው፡፡ “አሁንም የበፊቶቹ አይነቶች አሉ” ወደሚል ንቃት ተቀሰቀስኩኝ፡፡ በትጋት መከታተል አለብኝ ከእንግዲህ፡፡ ገጣሚዎች አሁንም አሉ፡፡ “ሀ ቢሞት “ለ” ይወለዳል፡፡ ውልደት ካለ ደግሞ ሞት አለ።

የበፊቱ አተያይ በመደጋገም ማርጀቱን ያሳየናል። ሲሞት ደግሞ ትክክለኛ ውልደት መኖሩ አረጋጋጭ ነው። ሄኖክ ወደ ሞት የሚያደላ አለመሆኑን “የሽንታችን ውጤት”፣ “እኔ ሰራሽ ሀውልት”፣ “ሐውልቱ ይበላ” የሚሉ ግጥሞቹ ገላጭ ናቸው፡፡

*የሆድ አምላክ __~ኄኖክ ስጦታው

*የሆድ አምላክ __~ኄኖክ ስጦታው

ለማግኘቱ፣ ለማጣቱ
ለመውዛቱ፣ ለመንጣቱ
“እንጀራ” ነው ለሀበሻ፣
“እህል ውኃ” ምክንያቱ፡፡

ሕልውናው የጸናበት፣
መወጣጫ መሰላሉ
“የሆድ አምላክ” ተቀብቷል፣
 ይገለጣል “በእህሉ!”
ለረገጠው መሬት ሳይሆን፣
ከእግሮቹ በታች ላለው
ለማይነካው ሲንጠራራ፣
ለሰማይ ነው የቀረበው፡፡
“እህል ውኃ” በሀበሻ፣
አምላካዊ ክብር ለብሶ
“በጡር አለው” ተሰቅዞ፣
 “በክቡር ነው” ተወድሶ
ተሰጥቶ ነው ለሰማያት፣
የሚዘራው ምድር ታርሶ
“የሆድ አምላክ” ካለበቱ፣
 ከእኛው ሀገር ምግብ ነግሦ፡፡

*        *        *

የት ነው ያለህ የሆድ አምላክ?!
ላነገሡህ ምን አደረክ?!
ላመለኩህ መች አጠገብክ?!
ምዕመንህ ጠኔ ጥሎት፣ የሚበላው ተቸግሮ
በእርጥባን መኖር በቅቶት፣ ሀገር ላገር ተዟዙሮ
“የሆድ አምላክ” እውነት ካለህ፣
እስቲ ይጥገብ ለዘንድሮ?!?
____________

2003 .
ኄኖክ ስጦታው፣ -ሞት የግጥም መድበል

2013 ኖቬምበር 10, እሑድ

“የቱባ ክር ጫፎች” ~~ኄኖክ ስጦታው

የቱባ ክር ጫፎች

________

ጥምጣመ - ውሥብሥብ፣ ሕይወት እንደ ድውር፤

ጫፉን ለመያዝ ነው፣ የሰው ልጅ የሚጥር፡፡

የተጠቀለለው. . . መፈታት ሲጀምር

መልሰህ ጠቅለው፤ ተተብትቦ እዳይቀር፡፡

የለውም ጫፍ ብሎ፣ ቆርጦ የሚጀምር፣

አራት ጫፍ ያገኛል፣ ክሩን ሲተረትር፡፡

ጫፍ መያዝ በጥሶ፤ በጥሶ መቌጠር

ኢትዮጵያን አርጓታል፤ የብዙ ጫፍ ሀገር፡፡

ሞልቷታል እምዬ፤ አያልቅም ቢቆጠር፣

አያሌ ጫፍ ወራጅ፣ ዕልፍ ቆርጦ - ጀምር፣

ተብትቦ የሚተው፣ ደህነኛውን ድውር፤

ለመፍታት ሲነሳ፣ ጠቅልሎ ማይጀምር፡፡

____________

12/10/2004.
~~ኄኖክ ስጦታው፣ -ሞት የግጥም መድበል

2013 ኦክቶበር 30, ረቡዕ

የተዘጉ አንደበቶች ______(ኄኖክ ሥጦታው)

የተዘጉ አንደበቶች
______(ኄኖክ ሥጦታው)

1ኛው ቀን
ዓያት - ዓየችው
ዘጋት - ዘጋችው !
ቤቱ ገባ፤ ቤቷ ገባች
በሩን ዘጋ፤ በሯን ዘጋች!
መሸ ፤ ነጋ
2ኛው ቀን -
እሱም ወጣ፤ እሷም ወጣች
እሱም ዓያት፤ እሷም ዓየች
ኮራ...ኮራች፤
እንዳላያት፤ እንዳላየች
ሄደ...ሄደች፡፡

3ኛው ቀን-
4ኛው ቀን-
5ኛው ወር-
6ኛው ወር...
ለውጥ የለም፤ ለውጥ አለ፤
ምንም የለም፤ ምንም አለ!
በተዘጉ አንደበቶች፣
ሊግባቡበት የቀለለ
የቀየሱት መንገድ አለ፡፡
በዝምታ ሚግባቡበት...
ፈጥረው ነበር
አንድ ነገር
ለሌላ ሰው ’ማይነገር፡፡
_____________________

ኄኖክ ሥጦታው - "-ሞት" የግጥም መጽሐፍ

አርዝም አደንድን ______(ኄኖክ ሥጦታው)


አርዝም አደንድን
______(ኄኖክ ሥጦታው)

ስሜት ልጓ በጠሰ፤ አስማት ዋለ ለምንዝር
በአርዝም አደንድን ድግምት፣ አቅም ተሰዋ ለግትር፡፡
መሰዋቱ ባልከፋ፣ ለዚያችኛዋ (‹‹ቂንጥር››)
አስማት ስሜት ታቅፎ፣ ካሸነፈው ያስማት ቀመር
ወንድነቱን ክዷልና ቀድሞውንም ወንድ አልነበር፡፡
______________
23-08-2005.

ኄኖክ ሥጦታው - "-ሞት" የግጥም መጽሐፍ

የቆሻሻ ወደብ ______(ኄኖክ ሥጦታው)

የቆሻሻ ወደብ
______(ኄኖክ ሥጦታው)

የስልጣኔ ዝቅጥ መጣያ፣ የጥራጊያቸው ወደብ ነን፤
የጣሉትን የምንለቅም፣ ካልጣሉልን የምንለምን፤
ፈረስም ነን ለነዚሁ፣ እንዳሻቸው የሚያደርጉን፤
ካሻቸው የሚለጉሙ፣ ካሻቸውም የሚጋልቡን፤
ካሻቸው የሚጭኑ፤ ካሻቸውም የሚዋጉብን፡፡

የገደልም ማሚቶዎች ነን፤ የጮኹትን የምንደግም፤
በለኮሱት ስንቃጠል፤ በቃ ሲሉን የምንከስም!

በስማ በለው ተብትበውን፣በቁሳቸውእንዳጨቁን፣
ስንዳክር ዳናው ጠፍቶን፣ እስከ መቼ እንዘልቃለን!?

ሲጋልቡን ስንጋለብ፣ የጫኑንን ስንሸከም፤
የጣሉትን ስንለቅም፣ የሚሉትን ስንደግም!
እንደ አራስ ልጅ በሰው ጀርባ
እስከ መቼስ እንዘልቃለን!?
እስከ መቼስ እንከርማለን!?
______________
መስከረም 2005.

ኄኖክ ሥጦታው - "-ሞት" የግጥም መጽሐፍ

2013 ኦክቶበር 25, ዓርብ

በእጅ ያልተቀረፀው የአበበ ቢቂላ ሐውልት - በግሱ - ከሀገረ-እንግሊዝ

በእጅ  ያልተቀረፀው የአበበ ቢቂላ ሐውልት




PDF


ልክ የዛሬ አርባ ዓመት፣ ከማራቶኑ አምበል ሻምበል አበበ ቢቂላ ቀብር መልስ፤ ኢትዮጵያዊው ባለቅኔ ጸጋዬ ገብረመድህን "አበበ እንጂ መቼ ሞተ!!" ሲል የፃፈው ሥነግጥም  እንዲህ ብሎ ይጀምራል፣ እንዲህ እያለ በዜማ ይፈሳል

በቅፅበት ፀንሶ ሞቱን
ድፍን አለም ደፍቶ አንገቱን                              
በልቡ ቀርፆት ፀሎቱን
በህሊናው ነድፎት ስሙን
በገፁ ፅላት ታሪኩን፡፡
አእዋፍን በደመና፣ ጀግናን በምድር ያስደነቀ
ማራቶን ጮራው ጠለቀ
                          በራሪው ኮከብ ወደቀ፡፡
በቃ ጀግናው ተከተተ
ይኸው የማይሞት ሰው ሞተ
ብለን አንበል እባካችሁ፤
 አበበ ተስፋ ነውና
ተስፋ አይቀበርምና፡፡

“ከእንጨት መርጦ ለታቦት፣ ከቃል መርጦ ለኪነት” እንዲል ስመጥሩ ብዕረኛ ዮሐንስ አድማሱ፤  በቅፅበት ፀንሶ ሞቱን የሚሉት የግጥሙ የመክፈቻ ቃላት የዚያን ታላቅ ሯጭ ህይወት በምልዐት ለመወከል የሚችል ጉልበት አላቸው፡፡  ቅፅበት ማለት ፍጥነት ነውና፤ አቤም ክብረወሰን ሰባሪ ፈጣን  አትሌት ነበረና። በሌላ በኩል ደግሞ እንደ ሩጫው ሁሉ ህይወቱም ቅፅበታዊ ነበረች፤ ብልጭ ብላ ድርግም ያለች። በራሪ ኮኮብ ነበረና፡፡ በነሐሴ 30 ቀን 1925 ዓ.ም በጃቶ ቀበሌ (ደብረብርሃን አውራጃ) እትብቱ ተቀብሮ፤ ጥቅምት 15 ቀን 1966 ዓ.ም አዲስ አበባ ላይ የመጨረሻ ትንፋሹን ሲጨልጥ፤ ገና አርባ አንድ አመቱ ነበር፡፡ ከአራት አመታት በላይ አሰቃይቶ ወደሞቱ የወሰደው ጎዳና አሁንም የፍጥነት ነገር አለበት -የቅፅበት! ሰሎሞን ተሠማ ጂ እንደሚከተለው ይተርከዋል፤

 “መጋቢት 14 ቀን 1961 ዓ.ም ቀትር ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አምስት ኪሎ ካምፓስ የአሁኖቹ የተማሪዎች መኖረያ ሕንፃዎች የተሠሩበት ቦታ ላይ መሠረት ለመጣል ጉድጓድ ተቆፍሮ ነበር፡፡ ሦስት የፖሊስ ባልደረቦችን ተኩስና ዱላ የሚሸሹ ተማሪዎች እየሮጡ የአበበ ቮልስ ላይ ሊወጡባት ተጠጓት፡፡ አበበ በፍጥነት መሪውን ጠመዘዘ፡፡ ሆኖም በስተቀኙ በኩል የነበረውን ለግንባታ የተቆፈረ ጉድጓድ አላስተዋለውም ነበር፡፡ ነገሮች በፍጥነት ተከሰቱ፡፡….. የአበበ አከርካሪ አጥንት (Spinal Cord) ተቀጨ፡፡”

ህይወትን በቅፅበት፤ በቅፅበትም ወደሞት፡፡ በቅፅበት ፀንሶ ሞቱን ማለት ይኼው ነው፤ በህይወት እና በሞት መካካል ልዩነት የሌለ እስኪመስል ድረስ። ታላቁ ከያኒ ገብረክርስቶስ ደስታ በስንኝ እንደተፈላሰፈው

በመኖር በመሞት
ልዩነት የሌለው
ቢኖርም ልዩነት
ከነፋስ ከውሃ መልኩ የቀጠነ
አይን የማይጨብጥው።
ህይወትን ሲያነቡት ወደግራ ሞት ነው።

በ1952 ዓ.ም የመጨረሻ ቀን የዕንቁጣጣሽ ዋዜማ ዕለት፤ ሮም ላይ በኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተንቆጥቁጦ፤ ይኼንንም ገድል ከአራት አመት በኋላ ቶኪዮ ላይ በመድገሙ -- ያውም ትርፍ አንጀት ለማስወጣት ቀዶ ጥገና ከአደረገ ስድስት ሳምንታት በኋላ! -- ብቻ አይመስለኝም አእዋፍን በደመና፣ ጀግናን በምድር ያስደነቁ  እግሮቹ በሞት ሲታበቱ፤ “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!!” ብለን እንድንል የጸጋዬ ብዕር የሚማፀነው። እርግጥ ነው አበበ አብቧል። ራሱን በእጥፍ ድርብ አባዝቷል። ከምሩፅ ይፍጠር እስከ መሃመድ አማን፤ ከደራርቱ ቱሉ እስከ ጥሩነሽ ዲባባ ድረስ ያሉትን የአገራችንን ውድ ልጆች ስፖርታዊ ድሎች ስንቆጥር፤ የአበበንም  ዘር ፍሬዎች አብረን እንቆጥራለን። ነገር ግን አበበ ቢቂላ ከሜዳሊያ ሠንጠረዥ በላይ ነው፣ በተራ አኃዝ ከቶም የማይለካ። ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው የአበቦችን ውበት ለማድነቅ የተጠቀሙበትን ሐረግ ልዋስና፤ አቤ “ከሥፍር ባሻገር’’ ነው።

ለምን ይሆን ግን አበበ ቢቂላ ምናባችንን ሰቅዞ የመያዝ አቅሙ ዘመን የማያደበዝዘው፣ የጊዜም ሂደት የማያበልዘው? ማራቶን በባዶ እግሩ  ሮጦ ማሸነፉን፥ በባዶ እግራቸው ቆንጥር ለቆንጥር ተፋልመው ነጻነታችንን በደማቸው በዋጁልን አባቶቻችን አምሳል ቀርፀን የጀግንነት ጥንፍ አርገን ማየታችን? ወይንስ ቢኒቶ ሙሶሊኒ ፋሺስታዊ ጦሩን ወደ ኢትዮጵያ በላከባቸው የሮም አደባባዮች፡ ቀጥ እና ኮራ ብሎ በድል አድራጊነት መንፈስ መሮጡን ባሰብን ቁጥር፥ ከቶም ሞቶ የማይሞተውን የአገር ፍቅር ስሜታችንን ማላወሱ? አሊያስ ለጥቁር አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ፣ በወቅቱ በቅኝ አገዛዝ ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩት አፍሪቃውያን ወንድሞቻችንን በ “ይቻላል” ስሜት  አንቅቶ፤ የልባቸውን መቅረዝ በተስፋ ዘይት መሙላቱን ከታሪክ ስላነበብን? ወይስ የአትሌቲስክ ድሎቻችንን ወደሌላ መስክ “መመንዘሩ” አንደማይገደን አልፎ አልፎ የሚታየን ጣፋጭ ራዕይ  ቀዳማዊ ደራሲ ስለሆነ?

“አበበ ተስፋ ነውና” የሚለው የጸጋዬ ሐረግ፤ ወዲ ቢቂላ ሯጭ ብቻ ሳይሆን የዘመኑ መንፈስ (zeitgeist) አብይ አካል እንደነበር ያመለክታል። ከአዝማሪ ቤቱ ሆይሆይታ (“ያገባሻል ያገባሻል፤ አበበ ቢቂላ ያገባሻል፤ጥላሁን ገሠሠ ይድርሻል’’ የሚለውን ህዝባዊ ዘፈን ያስታውሷል) እስከ ለውጥ አራማጅ የተማሪዎች ንቅናቄ ድረስ ያ ብጡል (mighty) አትሌት ስሙን ለድፍን አገር አውሶ ነበር። ለዚህ አባባል ማስረጃ ያህል፤ በኅዳር 1957 ዓ.ም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ለጀግናው አትሌት የክብር ግብዣ ባደረጉበት ዕለት፤ ትንታጉ ገጣሚ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ምነው አገራችን እንደአበበ ያሉ በርካታ ሁነኛ ሰዎች በኖራት በሚል የቁጭት መንፈስ “ኧረ የወንድ ያለህ!” ብሎ ካሰማው የብዕር እንጉርጉሮ  በጥቂቱ እንንጠቅ

ለወገኑ እሚቆጭ ሁለተኛ ሙሴ
አንደአበበ ያለ የማይል ለራሴ
ብታገኝ አገሬ ምንኛ ደስ ባላት ውስጣዊቷ ነፍሴ።
…..
እንዳበበ ያለ ጀግናና ጎበዝ ልጅ ቢኖር ኖሮ ለሀገር
የጎሳ ልዩነት መች ያናጥር ነበር?
የተዋረድ ኑሮስ መች ይሰፍን ነበር?
እውነትን ውሸት መች ያደባይ ነበር?
ፉራፉሬስ ሆነን መች እንዞር ነበር?

በየካቲት 1999 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ ቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ለአበበ ቢቂላ እና ለማሞ ወልዴ መታሰቢያ የቆሙት ሐውልቶች ባልታወቁ ወንጀለኞች እጅ መፍረሱ አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ዜና ሆኖ ነበር። ቢሆንም የአበበ ቢቂላ ገድል “ከሥፍር ባሻገር’’ ነውና፤ እልፍ አዕላፍ ዜጎች በእጅ ያልተቀረፁ በጊዜም ሆነ በውለታ ቢስ ወገን መዶሻ የማይናዱ ቋሚ ሐውልቶች በልባቸው ፅላት አኑረውለታል፡፡ ሩሲያዊው ገጣሚ አሌክሳንደር ፑሽኪን ለነገስታት እና ለምድር ኃያላን  ማስታወሻ ከቆሙት ግዙፍ ሐውልቶች ይልቅ፤ ለሰው ልጆች ነፃነት ወግኖ የጻፋቸው ግጥሞቹ በእጅ ያልተሰራና ከቶም የማይፈርስ ሐውልት ሆነው ዘመንን ተሻግረው እንደሚዘልቁ  የተነበየውን፤ አያልነህ ሙላቱ እንደዚህ አርጎ ወደ አማርኛ መልሶታል

ግርማ ሞገስ ያለው እጅግ የሚያኮራ
በእጅ ያልተቀረፀ በሰው ያልተሰራ
ሐውልት አቁሜያለሁ ለመታሰቢያዬ
ለሚመጣው ትውልድ ለወደ ኋላዬ።

ለአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ከቆሙ በእጅ ያልተቀረፁ ሐውልቶች መካከል፣ የጸጋዬ ገብረመድህን “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!” ሥነግጥም እጅግ ውቡ እና ጠንካራው ይመስለኛል።

                          የጎበዝ ነባቢት ነፍሱ
የሰው መዝርዕቱ አርአያ፤ የማይታጠፍ መንፈሱ
በጥራት የታጠፈለት፤ የምድር አጥናፍና አድማሱ
የየብስ የአየሩ ነበልባል
የማራቶን እፁብ አይጣል
የምድር አለሙ ገሞራ
አገሩን በክብር ያስጠራ
ሳተናው እግረ ጆቢራ
ሎጋ ቢቂላ ዋቅጂራ፤
የጎበዛዝ ንጥረ ወዙ
የተስፋ ብርሃን መቅረዙ።
ስሙን ላገር ስም ሰይሞ፤ የምስራች ያስደወለ
ስንቱን ስንቱን ልበ ሙሉ፤ ከአድማስ አድማስ ያስከተለ፡፡
የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ
ያረጋት የኦሎምፒክ አርማ
በወገኖቹ ልቦና፤ ቀና ኩራት ያሳደረ
እንደፍላፃ በአክናፉ፤ የአየርን ሰርጥ የሰበረ
የፍስሃዋን አዋጅ ለአለም፤ በአቅመ ወዙ ያስነገረ
በአገር ፍቅር ልቡን ሞልቶ፤ ላቡን ነጥቦ የዋተተ
የአለምን ጀግና በአድናቆት፤ በቅን ቅናት ያስሸፈተ
አልሞተም እንበል እባካችሁ፤ “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”        
            
ግሱ
ጥቅምት፤ 2006 ዓ.ም
ሀገረ-እንግሊዝ

(የወደር የለሹን አትሌት አርባኛ የሙት ዓመት፣  በባዶ እጅ ላለማዘከር የተደረገ ግለሰባዊ መፍጨርጨር)

2013 ኦክቶበር 24, ሐሙስ

አሸባሪው ማነው? --በኄኖክ ስጦታው

አሸባሪው ማነው?

በቀይዋ ብዕሬ፣ የከተብኩት ሁሉ፤
አንዴ ከኔ ወጥቷል፣ እስቲ ተቀበሉ።

እውነትን ሊናገር፣ አፉን የከፈተ፤
ንቅዘቶችን ነቅሶ፣ ድክመትን ያተተ፤
በዚህች ጉስቁል አገር፣ ምሣር በበዛባት፤
በሚቀጥለው ቀን፣ ለርሱ ወየውለት!!

ለምን!?
ፈራጅ ነው ዘራፊ፤ ተዘራፊው ሌባ
ትችት ያሳስራል፤ በማሸበር ደባ

የታል!?
"ነፃ አውጪው" የታል!?
ሆኗል ጨቋኝ መሪ
"ለምን" ባዩን ፈራጅ፤ "በሽብር ፈጣሪ"
ደፍሮ የሚናገር፣ ዘብጥያ ታሣሪ።

ማነው!?
ፀረ—ሠላም ማነው!? ማነውስ ነፃ አውጪ!?
አሸባሪ ማነው!? ማንኛው ነው ቀጪ!?
ወንጀለኛው ማነው!? ማነውስ ታሳሪ!?
ፀረ—ሠላም ከሣሽ፣ እራሱ መስካሪ፤
"ለምን" ባይ ተከሣሽ፣ ላገር ተቆርቋሪ!!

2004 ዓ. ም.


(ከ "ሀ-ሞት" የግጥም መጽሐፍ/ በኄኖክ ስጦታው)

ተጠየቁ ዳኞች! ~በ ኄኖክ ስጦታው —

ተጠየቁ ዳኞች!
  
~በ ኄኖክ ስጦታው —

ችሎት እንዴት ዋለ?!
          ማን ተፈረደበት?!
          ማንስ ተቀጠረ?!
ይህ ሁሉ እስረኛ ወኅኒ የታጎረ
በፍርዱ ረካ?! ወይስ ተማረረ?!
ተጠየቁ ዳኞች! መልሱልኝ እውነት….
የነገር ግራ ቀኝ፣ የምትመረምሩት
ግዜው ምን ያህል ነው?! ቀናት ወይስ ሳምንት?!
ዓመት ሁለት አመት?!
ሰምታችሁ ምትፈርዱት?!
ይግባኝ!
ይግባኝ!
ይግባኝ!
ይግባኝ ደረጃ አንድ፣ ይግባኝ ከፍተኛ
ይግባኝ ዐቃቤ ሕግ፣ ይግባኝ ሰሚ ዳኛ!
ተጠየቁ ዛሬ፣ መልሱልኝ እውነት
ግዜ አላችሁ ወይ ሰምታችሁ ለመፍረድ?!
ምን ያህሉ ሰው ነው ወኅኒ የተጣለ?!
ሰሚ ጆሮ አጥቶ ፍትህ ያልታደለ፡፡
ባላጠፋው ጥፋት በሀሰት ውንጀላ
ክርክር ረትቶት የአግቦ ፍተላ
“ይግባኝ!” ብሎ ሲጮኽ፣ “ልስማኽ” የማይሰኝ
ምን ያህል ነፍስ ነው፣ ወኅኒ ውስጥ የሚገኝ?!
ይግባኝ!
ይግባኝ!
ይግባኝ!
ይግባኝ ደረጃ አንድ፣ ይግባኝ ከፍተኛ
ይግባኝ ዐቃቤ ሕግ፣ ይግባኝ ሰሚ ዳኛ!
  
“ሀ -ሞት”  የግጥም መጽሐፍ
 ኄኖክ ስጦታው —


2013 ኦክቶበር 16, ረቡዕ

ትዝታ ዘ-ገብረ ክርስቶስ ደስታ ፡ ገጣሚ - ሰዓሊ? ወይስ ሰዓሊ - ገጣሚ? - በዶክተር ፍቃደ አዘዘ


ይህ ጽሑፍ በመጠኑም ቢሆን ስለገብረ ክርስቶስ ደስታ ማንነት የሚያትት ሆኖ ስላገኘሁት የዶክተር ፍቃደ አዘዘን ንግግር በፎቶ መልክ ገጼ ላይ ለጥፌዋለሁ፡፡ርግጥ ውይይቱ የተካሄደው የዛሬ አስር ዓመት ገደማ ቢሆንም ቅሉ ፣ ካለው ኪነጥበባዊ ፋይዳ አንጻር ለአጥኚዎች እንደ አንድ ግብዓት ማገልገሉ እሙን ነው፡፡ ውድ የእልፍኜ ታዳሚያን ፣ በገጣሚና ሰዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ ሥራዎች እና የሕይወት ጉዞ ላይ ተጨማሪ መረጃ ካላችሁ በኢሜል አድራሻዬ ትልኩልኝ ዘንድ መልካም ፍቃዳችሁን እለምናለሁ፡፡

[PDF]

 






2013 ሴፕቴምበር 20, ዓርብ

አላዋቂ ሳሚ . . . .! በ-ኄኖክ ስጦታው



የዚህ ጽሑፍ መነሻ ጳጉሜ 3 ቀን 2005ዓ.ም በዋልታ ኢንፎርሜሽን ድረ ገጽ ላይ “ሥነ-ጽሑፍ እና ትምክህተኝነት” በሚል ርዕር፣ “ቢላል” በሚል ብዕር ስም (ኋላ ላይ ማንነቱን የሚገልፅ ፍንጭ በመስጠት ማንነቱን የደረስኩበት ጸሐፊ) አማካኝነት የቀረበ ጅምላ ጨራሽ ዳሰሳ ነው፡፡

ርግጡን ለመናገር “ሥነ-ጽሑፍ እና ትምክህተኝነት” በተሰኘው ርዕስ ሥር ያለውን ጭብጥ ለመረዳት ጽሑፉን ደጋግሜ አንብቤዋለሁ፡፡ በዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ድረ-ገጽ ላይ መውጣቱ ትኩረቴን ባይስበው ኖሮ ተራ የስም ማጥፋት ድርጊት ነው ብዬ ባለፍኩት፡፡ እንዲህም የተቆርቋሪነት ስሜቴን ባላንጸባረቅኩ፡፡ ሆኖም እንዳሰብኩት አልሆነም፡፡ እናም ለውይይት ይሆን ዘንድ በር ከፈትኩ፡፡

ርግጥ ነው ጽሁፉ “ሥነ-ጽሑፍ እና ትምክህተኝነት” ርዕሱ ነው፡፡ አላማው እና ጭብጡ ግን ከሥነ-ጽሑፍም ባሻገር የጸሐፊውን ትምክህት በግልፅ የሚያሳይ፡፡ ሙሉ ሀተታውን በዚህ አድራሻ ያገኙታል፡- http://www.waltainfo.com/index.php/2011-09-07-11-57-06/10279-2013-09-08-20-31-21

ሀተታውን በማነብበት ሰዓት የተሰማኝን በመግለጽ ወደዋናው ጉዳይ ልግባ፡፡

ተጀመረ!

ከርዕሱ እንደምንረዳው “ሥነ-ጽሑፍ እና ትምክህተኝነት” ደፋር ርዕስ ነው፡፡ ምን ለማለት ነው እንዲህ አይነት ርዕስ የመረጠው?? በሚል ውስጣዊ ውዝግብ ፈጥሮ የመነበብን ጉልበት ይፈጥራል፡፡ “ሥነ-ጽሑፍ እንዴት ትምክህተኛ ይሆናል?? ትምክህተኛ እንዲሆንስ ማነው የሾመው?? ሥነ-ጽሑፍ የጽሑፍ ውበት ሆኖ ሳለስ እንዴት በትምክተኝነት ይፈረጃል??” በሚሉ መሰረታዊ ጥያቄዎች እየተናጥኩ አነበብኩት፡፡ በመጀመሪያው ንባቤ ርዕሱና ጭብጡ ተጣረሱብኝ፡፡


ጉድ እኮ ነው፡፡ “አንድ ሰው የተወሰኑ ጸሐፍትን ለመተንኮስ እንዴት ዙሪያ ጥምጥም ይጋልባል??” ብዬ ራሴን ጠየቅኩ፡፡ ለጥቆም፣ “ከተወሰኑ ጸሐፍት ባሻገር አገራዊ አጀንዳ ማንሳቱ ካልቀረ እንደምንስ ጭፍን ግንዛቤውን ልብ በሚደልቅ ርዕስ ይጀምራል??” የሚል አንፃራዊ ጥያቄ ወጥሮ ያዘኝ፡፡ ጉዳዩን ለመረዳት ለሶስተኛ ጊዜ አነበብኩት፡፡ ይህኔ ግን የተረዳሁት ይህን ነው፡፡ “እንዴት እራሱን “ዋልታ” ነኝ ምሎ የሰየመ የመረጃ ማዕከል እንዲህ ያለ ተልካሻ የስም ማጥፋት ዘመቻ በድረ-ገፁ ላይ ,ሊያስነብበን ፈለገ??” ወደሚል ጥያቄ ተሸጋገርኩ፡፡

መልስ ምት!!

የጽሑፉ ጭብጥ የማይነካካው ነገር የለም፡፡ ዓለም ስትፈጠር ጀምሮ የነበረውን የሥነ-ጽሑፍ ሂደት አሻሚ በሆነና በደፍናናው ሊነግረን ይሞክርና (መነሻውን አታውቅም ፣ አርፈህ ተቀመጥ እንዳንለው ነው መሰል¡) ነፃው ፕሬስ ፖለቲካዊ ተፅዕኖው ከአፍራሽ ፓርቲዎች ግፊት የመነጨ ነው ከማለት አንስቶ የግለሰቦችን ስም እየጠቀሰ “እከሌ ፀረ-ኢህአዴግ ነው፣ እከሌም ጨለምተኛ ነው ፣ እንቶኔ የቅንጅት ቅብርጥሶ ነው ፣ እከሌም የደርግ ወታደር ነበር . . .” የሚሉ ተልካሻ ሃሳቦችን አስደግፎ ከዓለም ዓቀፋዊ አጀንዳ ወደ አገራዊ አጀንዳ ፤ ከአገራዊ አጀንዳ ወደ ፖለቲካዊ አጀንዳ ፤ ከፖለቲካዊ አጀንዳ ወደ ግለ-ሰብዓዊ አጀንዳ፤ ከግለ-ሰብዓዊ አጀንዳ ወደ ግል ብሶት ይሸጋገርን እንዲያ ቀልባችንን የሳበውን ርዕስ የብሶት መወጫ ያደርገዋል፡፡

ከመጨረሻው ልጀምር!

ይህን ጭብጥ በ“የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ላይ የተቃጣ ጦር” ብዬ ሰይሜዋለሁ፡፡ የዚህ ጽሑፍ አጠናቃሪ፣ አቶ ሰለሞን ሽፈራው (ይቅርታ) አቶ “ቢላል” ፣ የደራሲያን ማህበሩ ያሉበትን መሰረታዊ ችግሮችን እና መፍትሔዎችን ከማመላከት ይልቅ ለርሳቸው የቀለላቸው፣ የማህበሩ አመራሮች እና አባላቶችን የፖለቲካ አቅዋም “በመናገር” በሌሎች ዘንድ ማሳጣት ነው፡፡

እዚህ ላይ እንዲሰመርበት የምፈልገው ነጥብ አለ፡፡ የዚህ መልስ ምት ጸሐፊ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር አይደለሁም፡፡ የኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ አካል ግን ነኝ፡፡ እንደ ብዙ ገለልተኝ ጸሐፍት የኢትዮጵያን ደራሲያን ማኅበር እንቅስቃሴ ድክመት ግን ለባለሙያው ሊሰጠው ከሚችል ድጋፍ አንጻር እያነሳሁ ከሚተቹ ሰውች አንዱ እንደሆንኩ አረጋግጣለሁ፡፡ ታዲያ አቶ ሰለሞን (ይቅርታ) አቶ “ቢላል” በጻፉት ትችት ላይ ለምን ቅሬታዬን አሰማለሁ?? . . . ነገሩ ወዲህ ነው፡፡

በአንድ ሙያዊ ማኅበር የታቀፉ ሥራ አስፈጻሚዎችም ሆኑ አባላት የፖለቲካ አመለካከት የማኅበሩ ጉዳይ እንዳልሆነ አምናለሁ፡፡ እንዳልኩት አንድ ነገር ያስማማናል ብዬ አምናለሁ፡፡ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር እንደ ሙያ ማኅበርነቱ መሥራት ያለበትን እንዳልሠራ ርግጥ ነው፡፡ (ወዳኋላ ተመልሰን ከዚህ ቀደም በነበሩ አመራሮች የተሠሩትን ማተት የርዕሰ ጉዳዩን መስመር ያስታልና መጥቀሱ ፋይዳቢስ በመሆኑ አልፌዋለሁ፡፡)

የአቶ ቢላል ሃተታ በደራሲ ማህበሩ የሚስተዋለውን ከአቅም በታች ያለን አተገባበር በማስረጃ አስደግፎ በማቅረግ መፍትሔውን እንደማመላከት ፣ የአባላቱን የፖለቲካ አቅዋም ላይ በመዘበት የደራሲያንን ብቃት በአንቶ ፈንቶ የመንደር ወሬ ጭቃ መቀባቱን ግን እቃወማለሁ፡፡ ተቋውሜንም እንዲህ እቀጥላለሁ፡፡ ልብ በሉልኝ፡፡ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር አባል አይደሉም፡፡ አለመሆኔ ግን የአቶ ቢላል (ይቅርታ) የአቶ ሰለሞንን ጽሑፍ ከመቃወም አያግደኝም፡፡ እንድቃወም ያደረገኝ ምክንያትም ይሄው ሚዛን በማይደፋ ማስረጃ የተጻፈ ጽሑፍ ነው፡፡

“የሥነ-ጽሑፍ ትምክህተኝነት” በሚል ርዕስ የተጻፈው ይህ ሀተታ፣ ከመነሻው ጀምሮ የሚስተዋሉበት መሰረታዊ እርስ ራሳቸው የሚጣረሱ አሉባልታዎችን መሠረተ-ቢስነት ማጋለጥ ግድ ነውና!

ጥያቄ 1

(ከዚህ በታች ለጻፍከው የቀረበ)

------------------------

“….የሀገራችን ስነፅሁፍ ዛሬም ከመቼውም ጊዜ በላይ ለጥላቻ ፖለቲካ ማራመጃ እየተደረገ እንደሚገኝ ተጨባጭ ማስረጃዎችን በዋቢነት እያጣቀስኩኝ ልቀጥል፡፡ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በዚህ ረገድ እያበረከተ ያለውን አሉታዊ አስተዋፅኦ ላስቀድምና ከዚያም ወደየአሁኖቹ “ደፋር” የግል ፕሬስ ውጤቶች እመለሳለሁ፡፡
በተለይም ከ1990ዎቹ መጀመሪያ ወዲህ በኢትዮጵያችን የስነፅሁፍ ታሪክ ውስጥ ተወልደው በማደግ ላይ ከሚገኙት ወጣት ደራሲያን መካከል፣ እንደለጌታ ከበደ አንዱ ነው፡፡ በዚህ መሰረትም የአንጋፋው የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ዋና ፀሐፊ ሆኖ ከተመረጠ ከስምንት ዐመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ እናም ይሄው ወጣት ደራሲያችን የሙያ፣ ማብሀሩ የሰጠውን ስልጣን በመተገን ስነፅሁፋችንን ጭፍን ጥላቻ ለተጠናወተው የፅንፈኛ ተቃዋሚዎች ድብቅ ዓላማ ማስፈፀሚያ ሊያደርገው የማይፈነቅለው የትምክህተኝነት ድንጋይ፣ የማይቆፍረው የጠባብነት ጉድጓድ፣ እንደሌለው በተደጋጋሚ መታዘቤን እነሆ ከዚህ እንደሚከተለው በተጨባጭ ምክንያታዊነት አስደግፌ አወጋችሁ ዘንድ እገደዳለሁ፡፡
ለወትሮው በተለያዩ የፈጠራ ፅሁፎቹ (አጫጭርና ወጥ የልቦለድ ድርሰቶቹ) የምናውቀው እንደለጌታ ከበደ “ፍትሕ” በሚል ርዕስ ይታተም ከነበረው የምፅዓት ቀንን ናፋቂ የግል ጋዜጣ ጀምሮ እስከአሁኑ “ፋክት” መፅሔት ድረስ የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጋሻ ጃግሬ እንደሆነ የዘለቀ ቋሚ የፀረ ኢህአዲግ ፅሁፍ አቅራቢ፣ ወይም “አምደኛ” ከመሆኑም ባሸገር፣ የደራሲያን ማህበር ዋና ፀሐፊነቱን ተተግኖ የሚፈፅመው ደባ ግን ከሁሉም የከፋና “ሀይ!” ሊባል የሚገባው አስነዋሪ ተግባር ሆኖ ነው ያገኘሁት፤ እኔ በግሌ፡፡
ለዚህ አባባሌ የተሻለ አብነት ሊሆነኝ የሚችለው ደግሞ፣ ህዳር 27 ቀን 2004 ዓ/ም “የዓባይ ዘመን” በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በብሔራዊ ቴያትር አዳራሽ አዘጋጅቶት የነበረው የኪነጥበብ መድረክ ነው፡፡
እንደእኔ እምነት ከሆነ በዚያ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴሩ ክቡር አቶ አሚን አብዱልቃድር በክብር እንግድነት ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ኪነጥበባዊ ዝግጅት ላይ፣ መድረክ መሪ የነበረው እንደለጌታ ከበደ ያሳየው እጅግ በጣም ቅጥያጣ ንቀት፣ የእርሱን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር አመራር አካላትና እንዲሁም ከበስተጀርባቸው ሆነው “ጎሽ..! የሚላቸውን ነውጥ ናፋቂ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጭምር የከፋ ትዝብት ላይ የሚጥል ቅንነት ማጣት ይመስለኛል፡፡ …..”

---------------------------

እኔ ምለው . . . ማኅበሩ የሚታማው በጥላቻ ፖለቲካ አራማጅነት ሳይሆን የገዢውን መንግስት በመደገፍ እንደሆነ ፀሐይ የሞቀው እውነት ነው፡፡ ታዲያ ይህን መንገር የአባላትን የፖለቲካ አቅዋም እንዴት ከማኅበሩ ጋር ማቆራኘት ተቻለህ??

ለመሆኑ፣ በዚህ ጥላቻ በሚዘራ አመለካከትህ ላይ ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ከአገራቸው ሳይሰደዱ፣ የክስ እና ውክቢያ ተፅዕኖን ተቋቁመው እየጻፉ ያሉትን ጋዜጠኞችን በደፍናናው ማበሻቀጥ ከስም ማጥፋት ወንጀል ተለይቶ የሚታይ ይመስልሃልን?? (ወይስ አንተም ሃሳብ የመግለጽ መብትህን ለዘለፋ እያዋልከው ነው??)

ኧረ ለመሆኑ፣ “ፀረ-ኢህአዲግ ናቸው” ማለት በአንተ መዝገበ-ቃላት ትርጓሜው ምን ይሆን?? የሥርዓት ብልሹነትን ነቅሶ ማውጣትና ድክመትን ማተት ኢ-ልማታዊ ሊያስብልስ እንዴት ይቻለዋል?? ልማታዊ ጸሐፊ መሆን ማለት እኮ የግድ መልካሙን ነገር ብቻ መልሶ መላልሶ ማተት አይደለም፡፡ የመናገር ነፃነት በማንቆለጳጰስ ላይ ብቻ ይገደብ ያለውስ ማነው??

“ምጽዓት ቀን ናፋቂ” ብለህ ያበሻቀጥካቸው ጋዜጠኞች እንደ ተስፋይቱ ምድር ኢትዮጵያም “ማር እና ወተት የሚፈልቅባት አገር ናት” ለምን አላሉም ብለህ ከሆነ ተሳስተሃል፡፡ እንኳን ከፊል ዲሞክራሲን ቆንጥራ በምታቀርበው አገራችን ቀርቶ የዲሞክራሲና መልካም አገዛዝ ማማ ላይ ተፈናጠናል በሚሉት ያደጉት አገራትም ብልሹ አሰራርን ተቃውመው የሚዘግቡ ጋዜጠኞች ይህ ስያሜ አልተሰጣቸውም፡፡

ጥያቄ 2
------------------------

“….ህዳር 27 ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር “በራሱ ተነሳሽነት” እንዳዘጋጀው እያንዳንዱ የአመራር አካላት በነቂስ የተናገረለትን ያን የድበበቆሸ መድረከ በአጋፋሪነት እንዲመራ በዝግጅት ኮሚቴው መመረጡን አስቀድሞ የነገረኝ ዋና ፀሐፊው እንዳለ ጌታ ከበደ፣ የዶ/ር በድሉን ማንነት ለታዳሚው ያስተዋወቀበት የወገንተኝነት ስሜትና አኔ መጨረሻ ላይ ወደ መድረከ ወጥቼ “ተወራራሽ ሕልሞች” በሚል ርዕስ የፃፍኩትን የህዳሴ ዘመን ግጥሜን ሳነብ ከየት እንደመጣሁ እንኳን ሊናገር አለመፈለጉ ምን ያህል ቅስሜን እነደሰበረውም በዚሀ አጋጣሚ ልገልፅለት እወዳለሁ፡፡….”

----------

ጸሀፊው (አቶ ሰለሞን) ይቅርታ (ቢላል) . . . ስለ ኢትዮጵያ ደራሲያን ሲያትት . . . እራሱን የማኅበሩ አባል እንደሆነ ጠቅሶ እንደ ሙያ ማኅበር ያለበትን ድክመት ሳይጠቅስ፣ የፖለቲካ አቅዋም እንደ አጀንዳ ማንሳቱ ለምን አስፈለገ?? “እከሌ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ነው፣ እንቶኔ “ፍትህ” ላይ ይጽፋል፣ በድሉ ‹እውነት ማለት . . .› የሚለው ግጥሙ ጨለምተኛ ነው፣ አባይ ግድብን አስመልክቶ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ልማት የሚያደናቅፍ ግጥም አነበበ፣ . . . እንዳለጌታ “. . . ወደ መድረከ ወጥቼ “ተወራራሽ ሕልሞች” በሚል ርዕስ የፃፍኩትን የህዳሴ ዘመን ግጥሜን ሳነብ ከየት እንደመጣሁ እንኳን ሊናገር አለመፈለጉ ምን ያህል ቅስሜን እነደሰበረውም በዚሀ አጋጣሚ ልገልፅለት እወዳለሁ፡፡” ማለትን ምን አመጣው??

የዚህ ሁሉ ሃተታ ፍፃሜ የጽሑፉን ጭብጥ የግል ቂም ከማስመሰል የዘለለ ፋይዳውስ ምንድነው??

እጅግ በሥራቸው አንቱ ያልናቸውን ጸሐፊያን ላይ ክብረ-ነክ በሆነ መንገድ ድንገት ተነስቶ መዘርጠጡ በራሱ ትምክህት አይደለምን??

2013 ኦገስት 31, ቅዳሜ

Reading Culture in Ethiopia. a paper presented in PEN Ethiopia International Conference


PEN ኢትዮጵያ ባዘጋጀው የመጀመሪያው የደራሲያን/ያት ዓለም አቀፋዊ ጉባዔ ላይ የቀረበ ነው፡፡ ሙሉውን ጽሑፍ በ ፒ.ዲ.ኤፍ ያገኙታል እና ቢያነቡት እወዳለሁ፡፡ ፔን ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ፔን አባል የሆነው በ2008(እ.ኤ.አ.) ሲሆን ከመጀመሪያው ብሔራዊ የጸሐፍት ጉባዔ ላይ “ንባብን ማስፋፋት” የተሰኘው ዘገባ ጉባኤ መጽሔት በሁለተኛው የጸሐፍት ጉባኤ በተሳተፍኩበት ወቅት እጄ ሊገባ ችሏል፡፡ በመጽሔቱ ላይ ያሉ መረጃዎች በስፋት ይነበቡ ዘንድ ከለኝ ጉጉት የተነሳም የባለሙያዎችን የጥናት ወረቀት በፒ.ዲ.ኤፍ ማግኘት እችል እንደሆን ለፔን ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ለአቶ ሰለሞን ኃ/ማርያም ጥያቄዬን አቅርቤ ስለተባበሩኝ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ ኄ.ስ 
   
  -----------------------------------

የማንበብ - መጻፍ ባህል በኢትዮጵያ ፡- አበረታችና አድካሚ አዝማሚያዎች


(አብርሃም ዓለሙ፤ አ.አ.ዩ)

ከአፍሪካውያን እይታ ልትደብቀው የምትፈልገውን ነገር መጽሐፍ ውስጥ አስቀምጠው” የሚል የፈረንጆች አባባል አለ፡፡ ማንበብ በአፍሪካውያን ሕይወት ውስጥ ምንም ቦታ እንደሌለው ለማመልከት የሚናገሩት ነው፤ 'አፍሪካውያን እና ንባብ አይተዋወቁም' ዓይነት ንቀት አዘል አስተያየትም ሊሆን ይችላል፡፡  . . . .

Reading Culture in Ethiopia. a paper presented in PEN Ethiopia International Conference 



2013 ኦገስት 16, ዓርብ

መርፌ ትሠራለህ? - ያልተፈታው ቅኔ (በ ግሱ)

መርፌ ትሠራለህ? - ያልተፈታው ቅኔ (በ ግሱ)

ስለአብዬ መንግሥቱ ቅኔ ሙያዊ ዳሰሳ ለአንባቢዎቼ እንዳካፍል በማሰብ ይህን ጽሑፍ ላደረስከን (ግሱ) ልባዊ ምስጋናዬ ይድረስህ፡፡ ውድ የእልፍኜ ተከታታዮች እና አንባቢያን ሙሉ ጽሁፉ በ ፒዲኤፍ ፋይል ከዚህ በታች ያገኙታል፡፡ መልካም ንባብ፡፡

ኄ.ስ  



merefe teseraleh?

2013 ጁላይ 24, ረቡዕ

የኔዋ ምርጥ ቮልስ /ዩሴን ቦልት/ በ-ኄኖክ ስጦታው


ከዚህ ቀደም በዚህቹ ጉደኛ ቮልስ መኪናዬ ዙሪያ በጥቂቱ አውርቼላችሁ ነበር፡፡፡ እስቲ ዛሬ ደግሞ ጥቂት ትውስታዎቼን ላካፍላችሁ፡፡

ያው መቼስ የቮልስ ባሉካ የሆንኩ ሰሞን የወረት ነገር በጥቂቱም ቢሆን ደባብሶኝ ነበር፡፡ መኪናዋን ማሽከርከር እንደጀመርኩ ወዳጅ ዘመዶቼን ሁሉ በመኪናዋ መስኮት ነበር ሰላም የምለው፡፡ መሬት የምረግጠው ከቤት ስወጣና እቤት ስገባ ነው፡፡ ቁርስ፣ ምሳ ፣እራት የምመገበው እዚህቹ መኪና ውስጥ ነበር፡፡ ጥቂት ጓደኞቼ በጣም ስናፍቃቸው ይደውሉና “ኧረ በጣም ናፍቀኸናል፤ መቼ ነው በአካል የምናገኝህ?” ይሉ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ በአካል እንደማያገኙኝ ቁርጡን ሲያውቁ ይህን ውሳኔ አስተላለፉ፡፡“በተገኘበት ቦታ ከመኪናው ላይ ተጎትቶ እንዲወርድ!!!” 

ደግነቱ እነሱ ጎትተው እኔን ከማውረዳቸው በፊት የፍሪሲዮን ካቦ ተበጠሰና ቮልሴን እያስጎተትኩ ጋራጅ ገባሁ፡፡ ያኔ በአካል ጋራጅ ድረስ መጥተው አገኙኝ፡፡ መኪናዋ ተሰርታ እስክታልቅ ድረስ ከጋራጅ አልወጣም ብዬ ነበር፡፡ ሜካኒኩ “ሲያልቅ እንጠራሀለን፡፡ በቃ፣ ሂድ” በማለቱና በእነሱ ጉትጎታ እጅግ አዝኜ ወጣሁ፡፡ መኪናዬ ተጠግና ስትወጣ በድጋሚ ጠፋሁባቸው ፡፡ 

ለቮልሴ የዘመኑን ሲዲ ማጫወቻ ያስገጠምኩላት ሰሞን ጓደኞቼ ብቻ ሳይሆኑ አገርም “ጉድ!” አለ፡፡ ጥቂቶች “ለቮልሱ ሲዲ ማጫወቻ ገጠመለት” አሉ፡፡ ብዙዎቹ ደግሞ “ለሲዲ ማጫወቻው ቮልስ ገጠመለት፡፡”

ከሁሉም የሚገርመኝ አንድ ሰሞን ወንድሜ ይነዳት ነበር፡፡ ከግቢ ውስጥ አውጥቶ መቶ ሜትር ያህል ያሽከረክርና የዋናው አስፓልት መንገድ ላይ አቁሞ በታክሲ ይንቀሳቀስ በነበረበት ሰሞን ይህቺው ቮልስ ቅፅል ስም ወጥቶላት ጠበቀኝ፡፡ እሱንም የነገረኝ ወንደሜ ነው፡፡ 

“እንዴት ናት ቮልሴ?” ብዬ ስጠይቀው፡-
“ምን እዚህ ሰፈር መች ያስነዱና!?? ቁጭ ብለው ቅፅል ስም መስጠት ነው ስራቸው፡፡ መኪናዋን ማን እንዳሏት አልሰማህም!? ” 
“ማን አሏት!?”
“ዩሴን ቦልት” 
እንደዚህ ጊዜ ስቄ አላውቅም፡፡ ወንድሜ መቶ ሜትር እየነዳ በመቶ ሜትር ጃማይካዊ ሯጭ ስም አስጠርቶልኝ አረፈው፡፡  

ይችው መኪና አንድ ከባድ ችግር አለባት፡፡ ጭንቀት አትችልም፡፡ ልብ ድካም ያለባት ይመስለኛል፡፡ በቃ፣ የተጨናነቀ አደባባይ መሀል ገባታ ቀጥ ነው! ጭንቀቷ ሌሎችን መኪና ይበልጥ እስኪያጨናንቅ ድረስ የአደባባዩን ውጥረቱን ታንረዋለች፡፡ እንደዚህ ሲሆን ከሶስት ያላነሱ ትራፊኮች ወደኔ ይመጣሉ፡፡ ያው ከቆመች መምጣታቸው እንደማይቀር ስለማውቅ የሞተር ቀሚሷን/ኮፈኗን/ ከፍቼ “ፖምፔታዋን/ ፊውል ፓምፕ” በውሃ እያቀዘቀዝኩ እጠብቃቸዋለሁ፡፡

“ከሥራ ክፉ ኩርኩር ግፉ” እንዲሉ . . . በጣም ጥቂት ሰው በቀር “መሀል አደባባይ ላይ ቮልስ ብንገፋ ስማችን ይጠፋል” ብለው ስለሚያስቡ ትራፊክ ፖሊስ እስኪመጣ ድረስ ከመጠበቅ በቀር አማራጭ እንደሌለኝ በሹፍርና አጭር ዘመኔ የቀሰምኩት ጥበብ ነው፡፡ ቮልስ ለመግፋት ዝንባሌ ያላቸው ጥቂቶቹም ቢሆኑ ከገፉ በኋላ እጃቸውን ዘርግተው በተራዬ ብር ወደነሱ እንድገፋ ስለሚጠይቁ አይመቹኝም፡፡ትራፊኮቹ ግን ገንዘብ የሚጠይቁኝ ሞተር ሲጠፋ ሳይሆን እኔ ሳጠፋ ነው፡፡ ከእነሱ ብዙዎቹ፣ “የቮልስ ሹፌር የሆነው በጣም ቢቸግረው ነው” ብለው ስለሚያስቡ መክረው የሚለቁ ናቸው፡፡ /አቦ መካሪ ትራፊክ አትጡማ/

እንደምንም ከተጨናነቀው መንገድ በተራፊክ እያስገፋሁ ልክ ነፃ መንገድ ሳገኝ ሞተሩ በራሱ ጊዜ ተረክ ብሎ ይነሳል፡፡  
  
የገዛኋት ሰሞን ባትሪዋ የኋላ መቀመጫ ስር ነበር፡፡ የመቀመጫው ታች ጥምዝምዝ ሽቦዎች አሉ፡፡ ከእነሱ በላይ እንደ እንቅብ የሚመስል የደረቀና የሳር ባህርይ ባለው ግብዓት መቀመጫው ተደልድሎ ጨርቅ ለብሷል፡፡ ይሄ ጥምዝምዝ ሽቦ ከመቀመጥ ብዛት በመላላቱ ሰው ሲቀመጥበት ወደ ባትሪው ወርዶ ከ“ኔጋቲሽ” እና ከ“ፖዘቲቭ” አካሉ ጋር እየተነካካ “ማሳ” (እሳት) ይፈጥራል፡፡ ይህን “ጥበብ” ያወቅኩት በተግባር ነው፡፡ ሁለት ጓደኞቼን . . . አንዱን ከፊት ሌላውን ከኋላ ጭኜ ስዘውር ከኋላ የተቀመጠው ጋደኛዬ በተረብ መልክ እንዲህ አለ፡-

“መቀመጫው በጣም ይሞቃል፡፡ ሃሃሃ . . . "ኤሲ" አስገጠምክለት እንዴ!?”

“ሞተሩ ከኋላ ስለሆነ ሙቀት ወደውስጥ ገብቶ ይሆናል፡፡” አልኩት በባለሙያ አገላለፅ ልበ ሙሉ ሆኜ፡፡

“አይመስለኝም” አለ እየትቁነጠነጠ፡፡ “ወደዳር አድርገውና እንየው፡፡ መቀመጥ አልቻልኩም . . .” እያለ ሳለ መኪናዋ ጨሰች፡፡ የኋላ በር እንኳን አልኖራት፡፡ ተፈጥፍጦ አንድ ነገር ይሆን ነበር ፡፡ድንጋጤ አስፈንጥሮ እላያችን ላይ ጣለው፡፡ እንዴት እንዳቆምን ትዝ አይለኝም፡፡ ጥቂት ሮጥ ሮጥ ብለንም ነበር፡፡ የሆኑ ሰዎች ለዚሁ ጉዳይ ያጠራቀሙት የሚመስል እጅግ የቆሸሸ ውሃ እያመጡ ወደውስጥ ይረጩ ጀመር፡፡ ብቻ እሳቱ "ወደሌሎች" ሳይዛመድ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ 

ታዲያ ያኔ (መኪናዋ እየተቃጠለች ሳለ) እኔ ባልለውም ዛሬ ድረስ እንዲህ ብሎ ነበር ይባላል፡፡ ውሃ እየደፉ እሳቱን ሊያጠፉ የሚረባረቡትን ሰዎች፡-

“ተውዋት! ትቃጠል! እኔንም እንዲህ ነበር ያቃጠለችኝ!!!”

2013 ጁላይ 22, ሰኞ

ውዝግብግብ …."ያላዘነው ውሻ እኔ ነበርኩ" በ-ኄኖክ ስጦታው





ዛሬ ደግሞ አንድ ወጣት ተሰቅሎ ሞተ፡፡ ወጪ ወራጁ ደረቱን በጆቹ ጠፍሮ መንሾካሾክና መረጃ መለዋወጥ ጀመረ፡፡ ሁሌም በሚሞት ሰው ላይ እንዲህ አይነት ነገር ይንፀባረቃል፡፡

“ቅድም ሰላም ብሎኝ ነበር ያለፈው፤ የሚሞት አይመስልም ነበርኮ” ትላለች አንዷ ለሌላዋ፡፡

 “ትላንት ከኛ ጋር ነበር ያመሸው፤ ምንም የተለየ ነገር አይታይበትም ነበር” ይላል ሌላው፡፡

“ሌሊት ውሻ ሲያላዝን ሰምቼ ደግሞ ማንን ሊገፋ ነው ይህ ሟርተኛ እያልኩ ሳስብ እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር ነጋ፡፡” አንዲት እናት ከጎናቸው ላሉ እኩያቸው ሲናገሩ ሰማሁ፡፡

ቀባሪዬ፣ እኔ ነኝ ውሻው፡፡ ሌሊት እንቅልፍ እንቢ ሲለኝ አላዘንኩ፡፡ እንደውሾቼ ጮህኩ፡፡ የሞት ጠረን ሸቶኝ ግን አልነበረም፡፡ ታንቆ መሞት ለዚህች መንደር አዲስ አይደለም፡፡ የሚሞት ባይኖር እንኳን የሚረዳ አይጠፋም፡፡ የጥሩንባ ድምፅና የውሻ ማላዘንን በሚፈራ ማህበረሰብ “የሞት መልእክተኛ” ተብዬ ለመፈረጅ ጊዜ አልፈጀብኝም፡፡ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ብቻ ውሻው እኔ እንደነበርኩ ሁሉም ነዋሪ አወቀ፡፡ ምሽት ላይ ከታጣቂዎች ጋር  ተፋጠጥኩ፡፡

“ሌሊት ስትጮህ ታይተሃል!” አለኝ አንዱ መሳሪያ ታጣቂ፡፡

“እና?”

“ምን “እና” ትላለህ? ለምን ሰላማዊ ሰውን ትረብሻለህ?” አፈጠጡብኝ፡፡

“እናንተ ለምን እኔን ትረብሻላችሁ?”

“ተነስ እንሂድ”

“አልነሳም!”

“መታሰር ትፈልጋለህ?” በሚያባብል ድምፀት ሌላው ተናገረ፡፡

“መታሰር ምንድነው?” መለስኩለት ጤነኛ እንዳልሆንኩ አንዴ ደምድመዋል፡፡ የትም ይዘውኝ ሊሄዱ እንደማይችሉ አውቃለሁ፡፡ ሊደበድቡኝ ይችላሉ፡፡ ሊያጠቁኝ አቅሙ አላቸው፡፡ ሰላማዊ ሰው ረብሼ ይሆናል፡፡ ለእኔ ግን ሰላማዊ ሰው በውሻ ድምፅ የሚረበሽ አይደለም፡፡ ቀድሞ እራሱን ባጉል እሳቤ የበጠበጠ ሰላማዊነቱ አይታየኝም፡፡

“አማኑኤል መግባት ትፈልጋለህ?” ብረት አንጋቹ ጠየቀኝ፡፡ የሱ ግንዛቤ አማኑኤልን ጥላቻ እዚህ የተቀመጥኩ መስሎት ይሆናል፡፡ ከዚህ የተሻለ ስፍራ ሊሆን ይችላል፡፡ ማገገሚያ አያስፈልገኝም፡፡ ግን ማየት ፈለኩ፡፡

“አዎ! አማኑኤል ውሰዱኝ!” ለመንኳቸው፡፡ ደጋግሜ ወተወትኳቸው፡፡ ማሰሪያ ገመዳቸው ተበጣጠሰ፡፡ አማኑኤልም ሊወስዱኝ አይችሉም፡፡ ታዲያ ለምን መጡ? ሊያስፈራሩኝ? ሊደበድቡኝ? እስኪሰለቹኝ ድረስ ኃይለ - ቃል ወረወሩብኝ፡፡ የማያደርጉትን ዛቱብኝ፡፡ ሰላማዊ ሰው ብረብሽ ከባድ እርምጃ እንደሚወሰድብኝ አስጠንቅቀው ነገሩኝ፡፡ በእነርሱ ዘንድ እብድ መሆኔ አስንቆኛል፡፡ በእኔ ዘንድ ሰላማዊ ሰው መሆናቸው አስንቋቸዋል፡፡ በመሰሎቻቸው ላይ የሚያደርሱት ቅጥቀጣ ለካስ እብድ መሆናቸውን ስላላመኑላቸው ነው! እብድ መሆኔን ማመናቸው ነፍስ ባጠፋም እንዳይፈርዱብኝ ያደርጋቸዋል፡፡ ምክንያቱም እብድ ነኛ! ህጉም ቢሆን ከጎኔ የሚቆመው ሰዎች ሰብአዊነቴን ስለሚዳፈሩ ሳይሆን ወንጀለኛ መሆን ስችል ብቻ ነው፡፡

 የሰላማዊነት ሎጅክ በነፍጥ አንጋች እና በኔ መካከል ልዩነት አለው፡፡ ዛሬ ባልጮህ ሰው አልበጠብጥም፡፡ ፍርሃታቸውን አልቆሰቁስም፡፡ አስተሳሰባቸው የወለደው ፍራቻ ይበቃቸዋል፡፡ ውሻ በጮኸ ቁጥር ግን ያስቡኛል፡፡ በኔ ላይ በሚጥሉት ሽርደዳ ሰላሜን ቢዳፈሩም እንቅልፍ አጥተው የሚፈሩትን ሞት አላስታውሳቸውም፡፡ ይህን ሳደርግላቸው ግን በመጮሄ የማገኘውን ሰላምን እየሰዋሁላቸው መሆኑን ይረዱት፡፡ እነሱም ይህ ውለታዬን አንድ ቀን ለመሬት ይከፍሉልኛል፡፡ ይሞታሉና!

አሽ-ሙጥ በ Henok Sitotaw

2013 ጁላይ 20, ቅዳሜ

ውዝግብግብ …. ዘዶሮ ማነቂያ /ከሌላኛው ምዕራፍ የተቀነጨበ/ --- በ-ኄኖክ ስጦታው




ውሾቼን ገደሏቸው! መርዝ የተቀባ ስጋ ሰጥተው ውሾቼን ገደሏቸው፡፡

ቀባሪዬ፣ መግደል እንጀራ በሆነበት አገር እንደመኖር ውስብስብ ነገር እንደሌለ ተረዳሁ፡፡ “ውሾች ለጤና ጠንቅ ናቸው” በሚል መርዝ አበሏቸው፡፡ ውሾች የመኖር መብት አላቸው፤ ፍጥረት ናቸውና፡፡ ባለቤት የሌላቸው መሆናቸው ግን አስገደላቸው፡፡ ልከላከል ሞክሬ ነበር፤ እንዳይበሉት ለማድረግ ጥሬ ነበር፤ ገዳዮቹን ለማባረር ጥሬ ነበር፤ ግን ብቻዬን ነኝ! ውሾቼኮ የበጋ ወዳጆቼ ናቸው፡፡ ይህ ክፉ ክረምት ውሾቼን ዳግም እንዳላያቸው የመሰናበቻ ጊዜ ሆነ፡፡ አለቀስኩ፣ ጮህኩ፣ ጉልበቴ ደክሟል፡፡ በጎረምሶች እጅ እግሬ ተይዟል፡፡

 የመንደሪቷ ነዋሪዎች የውሾቹን አሟሟት በማየት ለራሳቸው ደስታን ሲፈጥሩ እውነቴን ነው የምልህ ይበልጥ ጠላኋቸው፡፡ ለዚህች መንደር ነዋሪዎች የሞት ስቃይ ማየት የሚፈጥረውን ደስታ ማጣጣም አዲስ አይደለም፡፡ ሰዎች የሞት ቅጣት ይበየንባቸው የነበረበት ቦታ እዚህ መሆኑን እወቅ! ከብዙ ዓመታት በፊት የሞት ፍርደኞች በአደባባይ ይሰቀሉ እንደነበር ቦታ ላይ ነኝ፡፡ ይህ ታሪክ የማይረሳው ሰው በአደባባይ በሞትና በህይወት መሀል በነፍስ ከስጋ ለመለየት የሚደረግ መንፈራገጥን ምንነት የተገለጠበት ቦታ ነው፡፡ ይግባህ! የማወራው ድሮ ማነቂያ ስለነበር ስፍራ ነው፡፡ በክር አንገትህ ታንቆ መሞት ምን እንደሆነ የምታይበት ስፍራ፡፡ መንደሬን ያወካት መሰለኝ፡፡ ሞትን ወደህ ሳይሆን ተገደህ መጎንጨት ሰውን ሳይሆን የሞትን ክብር መንካት ነው፡፡

 መርዝ የተለወሰ ስጋ የበሉ ውሾች ሲዳከሙና ለሀጫቸውን ማዝረክረክ ሲጀምሩ ቦት ጫማና የጎማ ጓንት ያጠለቁ ገዳዮች በእጃቸው የያዙትን የብረት ማነቂያ አንገታቸው ውስጥ እየከተቱ አነቋቸው፡፡

ተፈጥሮ በህይወት ጉዞ ውስጥ ከለገሰቻቸው ሞቶች የበለጠ የሰዎች ፈጠራ ውጤት የሆነ የመግደያ ብልሃቶች ዘግናኝ ናቸው፡፡ ምስኪን….፣ ውሾቼ ሰዎችን ማመናቸው አሳዘነኝ፡፡ ትላንት በአደባባይ፣ ሊያውም በጠራራ ፀሐይ ጎዳና ላይ ሲተኙ ኮቴም ሆነ የመኪና ጥሩንባ አይቀሰቅሳቸውም ነበር፡፡ ሰው በመኖሩ ብቻ መኖር የቻሉ አድርገው የወሰዱ ይመስለኛል፡፡ ሰው ሳይኖር መኖር የሚሳነው ሰው ብቻ መሆኑን አውቀዋለሁ፡፡ ውሾቼ አለቁ! እንቁራሪቶቼም ለህፃናት መጫወቻ እየሆኑ ነው፡፡ ከሞት የተረፉትን በጋ ላይ አልሰማቸውም፡፡ የውሾቼ በድን መኪና ላይ ሲጫን የሞት ትርኢቱ ተደመደመ፡፡ የመንደሬ ለቅሞ አዳሪዎች ወደሬሳነት ተለውጠዋል፡፡ ገና ለገና አብደው ሰው የጎዳሉ በሚል ፍራቻ የመኖር መብታቸውን አጡ፡፡ አንድ ቀን እኔም `ጭራቅ” ሆኜ ደማቸውን እንዳልመጥ ይገድሉኝ ይሆናል፡፡ እጅ እግሬን ጠፍረው ይዘውኝ የነበሩ ወጣቶች ለቀውኝ ሄደዋል፡፡ ምሽት ብርታት እስቲሰጠኝ ባለሁበት መቆየትን መረጥኩ፡፡

ቀባሪዬ፣ ይህች የሰዎች ታንቆ መሞቻ መንደር ከስሟ ጀምሮ የብቻዬ እንጉርጉሮ እንዲያገረሽ አደረገብኝ፡፡

አንቺ ዶሮ ማነቂያ የሆንሽው ዶሮ ማነቂያ ሆይ! ዛሬ ምኒሊክ አደባባይ የሆነው ስፍራሽ ላይ የነበረው ትልቅ ዋርካ ይታየኛል፡፡ ያን ጊዜ አለመፈጠሬ ዋርካሽ በፈረሰኛው ምንሊክ ሃወልት ቢተካም፣ የግሪኮች ጣሪያ አልባ (አንፊ) ቴአትር የመሰለው ዘመንሽን ውስጤ በከሰተልኝ ዋርካሽ የጥቁር ብካይ ሂደትሽ ይታየኛል፡፡ አንቆ መግደልን “ፍትህ” ነው ብለው የሚያምኑ ነገሥታቶችሽ አጣብተውሽ ከሄዱት ክፉ ባህርይ ጋር ዛሬም ያው መሆንሽ፣ ዛሬም ማነቂያ መሆንሽን አወጋሻለሁ፡፡

2013 ጁላይ 19, ዓርብ

ብሌንን ያስታወሰኝ “ንቅሳት” ወ “ንክሳት” - ኄኖክ ስጦታው



ካፌ ውስጥ ነኝ፡፡ አንድ ሰው ከፊቴ እጀ ጉርድ ካናቴራ አድርጎ ካፑቺኖውን ይጠጣል፡፡ ቡና ከረባቴን አዝዤ ሰውየው ላይ አፈጠጥኩ፡፡ በእጆቹ ክንዶች ላይ ተነቅሷል፤ ተነቃቅሷል፡፡

በደህና ጊዜ የረሳሁትን “ታቱ”ዬን አስታወሰኝ፡፡

የንቅሳት ጠበብት ፡- “ንቅሳት ዘመን የማይሽረው ውጨ-ተውብሆ ነው” ይላሉ፤ ሊሆን ይችላል፡፡ እናቴ አንገቷ ላይ ተነቅሳለች፤ የአጎቴ ልጅ ደግሞ ድዱ ላይ ጉራማይሌ ተነቅሷል፡፡ እኔ . . . ሃሃሃ . . . ክንዴ ላይ ተነቅሼ ነበር፡፡ ጓደኞቼ ንቅሳቴን ዓይተው “ተነክሰህ ነው ተነቅሰህ?!” እያሉ ሲያላግጡብኝ አስፈግፍጌ አስጠፋሁት፡፡ /አስጠበስኩት ብል ይቀለኛል፡፡/ ጥሎት ያለፈውን ጠባሳ ስመለከት እውነታቸውን እንደሆነ አረጋግጣለሁ፡፡ አሁን ነዋ ከንቅሳትነቱ በላይ ንክሳት እንደሆነ የሚያስታውቀው፡፡
  
ሰውየው….
በእጆቹ ክንዶች ላይ ተነቅሷል፤ ተነቃቅሷል፡፡ በቅጥልጥል የእንግሊዘኛ ፊደል የተጻፈ ነው፡፡ ትርጉሙን ለመረዳት ለማንበብ ሞክሬ አልተሳካልኝም፡፡ እንኳን ተቀጣጥሎ እንዲሁ በ“ARIAL font” ተጽፎም አይነበብልኝም፡፡

 የድሮው ንቅሳት አንገት እና ጥርስ ብሎም ግንባር እና አገጭ ተኮር ነበር፡፡ ዘመንኛው ንቅሳት ጥቂት የማሸጋሸግ ሂደት ይስተዋልበታል፡፡ አንገት ላይ የነበረው፣ ወደ ደረት . . . ድድ ላይ የነበረው ወደጆሮ ግንድ  . . . የተጨመሩት ደግሞ፣   ጀርባ ላይ እና እምብርት ላይ ያሉት ናቸው፡፡ /ዘለቅ ብዬ አላየሁም እንጂ ሌላም፣ ሌላም ቦታ ላይ ተነቅሰው ይሆናል፡፡/

ንቅሳታሙን ሰው ምን እንደተነቀሰና ለምን እንደተነቀሰ ልጠይቀው አሰብኩ፡፡ ግን፣ ምንስ ቢነቀስ እኔ ምን አገባኝ?? አልኩና ተውኩት፡፡  ለምን ጥያቄውን ከእራሴው አልጀምርም፡፡እኔ ለምን ነበር የተነቀስኩት?!

“ብሌን” የተባለች ቆንጆ ወደድኩና ተነቀስኩ፡፡ የተነቀስኩ ሰሞን ከቅጥነቴ የተነሳ “ቆዳ ቅብ” አይት ነበርኩ፡፡ ታቱ የሠራልኝ ሰው ብዙ  አሪፍ አሪፍ ዓይነት አማራጭ ምስሎች ነበሩት፡፡ ግን ምኔ ላይ ይንቀሰኝ?? አልወደድኩትም እንጂ የሚመጥነኝ “ታቱ” አግኝቶልኝ ነበር፡፡ ልክ እንደ እጅ አምባር ሆኖ ክንድ ላይ የሚነቀስ፡፡ ትርጉም አልባ ነገር ከመነቀስ እስከነአካቴው አለመነቀስ ይሻላል፡፡ “ብሌን” ብለህ ነቅሰኘኝ አልኩት፡፡ ነቃሹ “አይሆንም” ብሎ ሞገተኝ፡፡ “ብሌን” ሶስት ፊደላት ነው፡፡ ክንድህ ደግሞ ወደታች እንጂ ወደጎን ቦታ የለውም፡፡ ስለዚህ “የዓይን ምስል” ይሻልሃል፡፡ አለና አሳመነኝ፡፡ ተነቀስኩ፡፡ የንቅሳቴ ቀለም ባግባቡ ሳያጠግግ ከብሌን ጋር ተለያየን፡፡ እንዴት እንደተለያየን አላውቅም፡፡ ስጠረጥር ግን “ለምን የአባቴን ስም አብረህ አልተነቀስክም??” በሚል አኩርፋኝ ሊሆን እንደሚችል እጠረጥራለሁ፡፡

እና አሁን በካፌ ውስጥ ካፑቺኖ የሚጠጣውን ሰው ሰውነት እና ቅጥልጥል የበዛበት ንቅሳት ሳስብ አንድ ነገር ተገለፀልኝ፡፡ ይህን ጊዜ እኮ “ብሌን ኃይለ ማርያም” ብሎ ይሆናል የተነቀሰው!

አንተ ሰውዬ፤ ልብ በል!!   “ንቅሳት ዘመን የማይሽረው መዋቢያ ቢሆንም ለተነቃሹ ግን ልዩ ምልክት ነው፡፡”


2013 ጁላይ 15, ሰኞ

“የፒያሳ አመልህን ይዘህ ቦሌ አትሂድ” - ኄኖክ ስጦታው



ወደ ቦሌ አካባቢ ሄደህ ፣ መዝናናት ካማረህ እባክህን ከማጨብጨብ ተቆጠብ፡፡

ከእለታት በአንድ የተረገመች ቀን እንዲህ ሆንኩላችሁ፡፡ ደምበል አካባቢ ካለው “ላ ፓራዚያን ካፌ” እግር ጥሎኝ ገባሁ፡፡ ከውስጥ መግባት ፈርቼ ወይም ሸሽቼ ከበረንዳው በስተቀኝ ወዳለችው የመናፈሻ ሳምፕል ወደመሰለችኝ “መናፈሻ” ገብቼ ተቀመጥኩ፡፡ ለደቂቃዎች ዞር ብሎ የሚያየኝ አስተናጋጅ አጣሁና በጭብጨባ ለመጥራት እጄን ማፋተግ ጀመርኩ፡፡ ያው …. ፒያሳ የለመደብኝ አመሌ አገረሸ፡፡

/ፒያሳ እኮ ካላጨበጨብክ የሚታዘዝህ አስተናጋጅ ጥቂት ነው፡፡ ኧረ አንዳንዴማ፣ አስተናጋጅ ለመጥራት ልታፏጭ ሁሉ ትችላለህ፡፡ የምመክርህ ነገር ቢኖር የፒያሳ አመልህን ይዘህ ቦሌ አትሂድ ፡፡/

ይህ አመሌ አገሸና ማጨብጨብ ጀመርኩ፡፡ አጨበጨብኩ፡፡ ዝም!
ደጋግሜ አጨበጨብኩ፡፡ ጭጭ!

የጭብጨባዬ ድምጽ “ላውድ” ላይ አድርጌ ቀወጥኩት፡፡ አሁን ዘዴዬ ሠራ መሰል አንዲት አስተናጋጅ መጣችና ቁልቁል በመመልከት “ምን ይጠበስ?!?” በሚል አስተያየት ታየኝ ጀመር፡፡

“ምንድን ነው?! ሳጨበጭብ አትሰሙም እንዴ!??!” አልኩ ቁጣ ባጠቃው ድምፀት፡፡

“ይኸው ልጨፍር መጣሁ እኮ!!” አለች እጆቿን ወገቧ ላይ አድርጋ፣ ትከሻዋንም “እስከስ” እያደረገች፡፡

ኧረ፣ መውረግረግ!!!


ምነው እጄን በቆረጠው! ምነው አቅሜን አውቄ እዛው ፒያሳ ባጨበጭብ!! ሃሃሃ /ባላጨበጭብስ/

2013 ጁላይ 13, ቅዳሜ

የጋሽ ሙኼ የአኗኗር ዘይቤ እና ብር ብር የሚሸቱ አባባሎች - ኄኖክ ስጦታው



ጋሽ ሙኼ “ወጪ ቆጣቢ ናቸው” ፡፡ ቁርስ ቤታቸው በልተው ይወጣሉ፡፡ ምሳቸውን ደግሞ አንዱ ምግብ ቤት/ረከስ ያለ ዋጋ ካለበት/ ይመገባሉ፡፡ ሁሌም ታዲያ አንድ አይነት ምግብ ነው የሚያዙት፡፡ ፍርፍር!!

ጥብስ ፍርፍርም ሆነ ቋንጣ ፍርፍር አይወዱም፡፡ /አይመቻቸውም ማለት የሚቀል ይመስለኛል፡፡/ የፆም ፍርፍር ብቻ!

/ከጨጓራ ህመም ማስታገሻ መድሃኒት አቅም እንኳን ርከሹን ነው የሚገዙት፡፡ በተለይ እንደ ጉንፋን ከረሜላ የምትመጠጠዋ ኪኒና እንደ “ገንዘብ” ነው የሚወዷት፡፡/

ጋሽ ሙኼ ብራም ናቸው፡፡ ብራቸው አንዴ ወደ ኪሳቸው ከገባ በድጋሚ ከኪሳቸው የሚወጣው ባንክ ቤት ውስጥ ብቻ ይመስለኛል፡፡ ለሥራ ጉዳይ ቢሯቸው በጠዋት ሄጄ ካጣኋቸው ፣ በቃ ባንክ ቤት ሄደዋል ማለት ነው፡፡ ማውጣትማ ሞታቸው ነው፡፡ ባንክ ቤት ገንዘብ ካላስገቡ ቀኑ ይጨልምባቸዋል፡፡ ሰው ያስጠላቸዋል፡፡ እንዲያ የሚያፈቅሩትን ፍርፍር ገበታ ላይ ማየት ያስጠላቸዋል፡፡

ባገኙኝ ቁጥር አንድ ጥያቄ አላቸው፡-

“ምን ይዘህልኝ መጣህ??” ይሉኛል፡፡

ይህ ጥያቄያቸው ወደአማርኛ ሲተረጎም “ብር ይዘህ መጥተሃል ወይ?” ማለት ነው፡፡ ያው፣ ቀብድም ይሁን ቀሪ ክፍያ መያዝ አለብኝ፡፡ የሚከፈል ነገር ከሌለ ደግሞ ወደፊት ከማሠራው ሥራ ላይ የሚታሰብ ብር ቆጥሬ መስጠት አለብኝ፡፡ ምንም ከሌለኝ ግን ቁጣቸውን የመቋቋም አቅም ሊኖረኝ የግድ ነው፡፡

“ባዶ እጅህን አትምጣ አላልኩህም?!!?” ይላሉ ሠራተኞች እየሰሙ፡፡

“ለሰላምታም ቢሆን መምጣት አልችልም?!?”

“በደረቁ ሰላም ብትለኝ ምንም አይጠቅመኝም፡፡”

“ሁለተኛ አልመጣብዎትም” ብዬ ልወጣ ፊቴን ሳዞር እንደልጅ አባብለው ወደ ካፌ ይወስዱኝና ይመክሩኛል፡፡ /ሃሃሃ… “ይመክሩኛል” የሚለው ቃል አባታዊነትን እንዲወክል ሆን ተብሎ የገባ ቃል እንደሆነ ታሳቢ ተደርጎ ይነበብልኝ፡፡/

“ይህችን ምክር ስማ” ይሉና ይጀምራሉ፡፡

“በእርጅና ዘመን እንዲሆንህ ተስፋ
ገንዘብ ኪስህ ካለ፣ ኪሶችህን ስፋ”

ገንዘብ ላይ ቢስቆነቆኑም በሌላ ነገር ደግ ናቸው፡፡ “ስነቃል” ሲያጽፉኝ መሰሰት የሚባል ነገር አያውቁም፡፡ ለዚህም ነው መሰል ብር ባይኖረኝም እንኳን “ምን ይዘህልኝ መጣህ??” እንደምባል እያወቅኩ እሳቸው ዘንድ እማልጠፋው፡፡

“ሃብታም ማለት . . .” ይሉኛል “ሃብታም ማለት ፣ ብዙ ገቢ ያለው ሳይሆን ካገኘው ላይ ብዙ የሚቆጥብ ነው፡፡”

“እንደ እርሶ ማለት ነው” እላለሁ በሆዴ፡፡

“ሀብታም መሆን ከፈለግክ እጅህን ቶሎቶሎ ኪስህ አትክተት” ይሉኛል፡፡

“እንደ እርሶ ማለት ነው” እላለሁ - በሆዴ፡፡

በሚያሳዝን ሁኔታ የብዙ ሰው ምክር ሰምቼ ተሳክቶልኛል፡፡ የጋሽ ሙኼ ምክሮችን ለመተግበር ግን ሳልችል ቀርቻለሁ፡፡ እንኳን ብር ኖሮኝ ባይኖረኝም እንኳን፣ እጄ ልምድ ሆኖበት ኪሴን ያፈቅረዋል፡፡

ግልባጭ ፡- አሽ-ሙጥ በ Henok Sitotaw

2013 ጁላይ 5, ዓርብ

ውዝግብግብ -- በ ኄኖክ ስጦታው


የውዝግብግብ ምናቦች ንሸጣዬ ሲበረታ እየቀነጨብኩ የማስነብባችሁ ነው፡፡ ሌላኛውን ምልከታ በሌላ ጊዜ …..

………. የተቀነጨበ…….

የጥቁርና ነጭ ቤቶችበምርጧመንደሬ ትከሻ ለትከሻ ተደጋግፈው ያንተን መምጣት ይጠባበቃሉ፡፡ በዚህች መንደሬ ሲመሽ ብቻ የሚታዩህ አነዚህ መጠጥ ቤቶች የግድግዳቸው ቀለም ጥቁርና ነጭ መሆኑ ለምን እንደሆነ ሁሌ ያሳስበኛል፡፡

ሴተኛ አዳሪዎች የገንዘብ ዕድገት ሲያገኙ የሚከፍቷቸው እነዚህ ቤቶች በድራፍት ራሱን ባሟሟቀ ጠጪ ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላ የሚደምቁ ናቸው፡፡ ቀባሪዬ አነዚህ ቤቶች የሚሰየሙት በሴተኛ አዳሪዋ ስም ነው፡፡አበዛሽ ፐብ” “ሣራ ፐብ”… የስም አይነት ታነባለህ፡፡ ሴቶችም ላያዊ ውበታቸው ወንዶችን የሚያማልል ዓይነት ቢጤ ነው፡፡

በእንደዚህ አይነት ቤቶች ለመዝናናት ኪስህን መተማመን ይኖርብሃል፡፡ ሴቶችም የዋዛ እንዳልሆኑ እንተን መስዬ እኖር በነበረ ጊዜ አውቀዋለሁ፡፡ ግራ እንደገባኝ የሚኖረው ግን እኝህ ቤቶች የተቀቡት ቀለም ነው፡፡ አንዳንዴ በውስጤ ጥቁርና ነጭ መሆኑ በደስታና ሀዘን ልፈታው እሞክራለሁ፡፡ መቼስ ሴቶቹ ሀሳቤን ቢሰሙ በእብደቴ እንደሚደሰቱ አምናለሁ፡፡

እርግጥ ነው ጊዜያዊ ደስታ የማያልፍ መከራን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ይህን ስልህ በሽታ ሸምተህ ትወጣለህ እያልኩህ ልደሰኩርልህ አይደለም፡፡ የዚህች መንደር ሴት አዳሪዎች ኤድስ ምን እንደሆነ ካንተ የበለጠ ያውቃሉ፡፡ ኮንዶም የህይወት ከለላቸው አድርገው ይኖራሉ፡፡ ዛሬ ለእነሱ በኮንዶም ስለ መጠቀም ልታስተምራቸው አትችልም፡፡ ላንተ ግን ያስተምሩሃል፡፡

የሴት አዳሪዎች ትልቁ ችሎታ አንተንም ሆነ ሌላውን እኩል የማስተናገድ ብቃትን መያዛቸው ነው፡፡ ገንዘብ ይኑርህ እንጂ ሁሉም ነገር ያንተ ነው፡፡ ፈገግታቸውን አይሰስቱብህም፡፡ ክፈልበት እንጂ ቢራም ሆነ ውስኪ ቀምሰው ይባርኩልሃል፡፡ የሴት አዳሪ ክብርን በግልፅ ታይበታለህ፡፡ አዎ! እራሳቸውን የሚያከብሩ እንጅ ራሳቸውን አፍቃሪ መሆናቸውን ለማወቅ ጊዜ አይፈጅብህም፡፡ ሥጋቸውን ሸጠው ያተርፉብሃል፡፡ አልኮል ሸጠው ያተርፉብሃል:: ቤተኛ ከሆንክ ደግሞ አንተኑ ከነነፍስህ ሸጠው ያተርፉብሃል፡፡ ለእነሱ ቢዝነስሽርሙጥናነው፡፡ ውበት ኃላፊ መሆኑን ካንተ በላይ ያውቁታል፡፡ ስለዚህም በጊዜ ቋሚ ንብረት ያላቸው ሴት አዳሪዎች ሆነዋል፡፡