2012 ዲሴምበር 8, ቅዳሜ

ሃ ገ ሬ በ ገብረክርስቶስ ደስታ



ሃ ገ ሬ
{ሰአሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ}

አገሬ ውበት ነው፣

ለምለምና ነፋስ የሚጫወትበት፣

ፀሃይ የሞላበት፣ ቀለም የሞላበት።

አገሬ ቆላ ነው፣ ደጋ ወይና ደጋ፣

እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ እስኪነጋ።

አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ፣

አገሬ ጅረት ነው ገደልና ሜዳ፣

ውበት ነው በበጋ ፀሃይ አትፋጅም፣

ክረምቱም አይበርድም፣

አይበርድም፣ አይበርድም። 

አገሬ ጫካ ነው፣

እንሰሳት አራዊት የሚፈነጩበት፣

በወጥመድ ሳይገቡ ሳይነካቸው ጠላት።

እዚያ አለ ነፃነት፣

የቆጥ ላይ ቅስቀሳ 2


2012 ዲሴምበር 5, ረቡዕ

NILE: A Poem by Tsegaye Gebre-Medhin



I am the first Earth Mother of all fertility
I am the Source I am the Nile I am the African I am the beginning
O Arabia, how could you so conveniently have forgotten
While your breath still hangs upon the threads of my springs
O Egypt, you prodigal daughter born from my first love
I am your Queen of the endless fresh waters
Who rested my head upon the arms of Narmer Ka Menes
When we joined in one our Upper and Lower Lands to create you
bosom of my being
How could you so conveniently count down
In miserable billions of petty cubic yards
The eternal drops of my life giving Nile to you
Beginning long before the earth fell from the eye ball of heaven,
O Nile, that gush out from my breath of life
Upon the throats of the billions of the Earth's thirsty multitudes,
O World, how could you so conveniently have forgotten
That I, your first fountain, I your ever Ethiopia
I your first life still survive for you?

በሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ/ እኔ እወድሻለሁ


ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚሊዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንችን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ።
እኔ እወድሻለሁ
የሰማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ፅጌ-ረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደ ሎሚ ሽታ፡፡
እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
እኔ እወድሻለሁ፣
አበባ እንዳየ ንብ፡፡