2017 ጃንዋሪ 5, ሐሙስ

“ጠጣህብኝ”!

አንድ እጅግ ያዘነ ሰው ባር ውስጥ ተቀመጦ ፊት ለፊቱ ያለውን መጠጥ ላይ እንዳተኮረ ሰላሳ ደቂቃ በላይ ቆየ። በዚህ መሐል አንድ ጠጪ ወደርሱ ቀርቦ ጠረጴዛው ላይ ያለውን መጠጥ አንስቶ ሻት አደረገው።

ምስኪኑ ሰው ስቅስቅ ብሎ ማልቀስ ጀመረ። “ተረጋጋ ወንድሜ፣ ለጨዋታ ነው  የጣሁብህ። ሌላ መጠጥ አዝልሃለሁ” ሲል ሊያረጋጋው ሞከረ።

“ነገሩ አልገባህም፣ ዛሬ ለእኔ ሲበዛ በመከራ የተሞላ ቀን ነው። ጠዋት መስሪያ ቤት ስብሰባ ላይ ጥቂት ደቂቃ አርፍጄ ብገኝ አለቃዬ ከስራዬ አሰናበተኝ። ወደ ቤት ለመመለስ መኪናዬን ወዳቆምኩባት ቦታ አመራሁ። በቦታው ግን አልነበረችም። መኪናዬ ተሰርቃ ነበር።  ለፖሊስ አመለከትኩ። እነሱ ግን ምንም ሊረዱኝ እንደማይችሉ ገልፀው አሰናበቱኝ። በጣም እያዘብኩ በኮንትራት ታክሲ ወደቤት ስመለስ ሞባይሌና የእጅ ቦርሳዬን ረስቼው ወረድኩ። ከዚህ ሁሉ መከራ ልታፅናናኝ የምትችለው ባለቤቴ ብቻ ነበረች። እሷም ቤት ስገባ ከአትክልተኛችን ጋር አልጋ ላይ ተኝተው ደረስኩ። ነገሮች ሁሉ ከአቅሜ በላይ ሆኑ። በመጨረሻ ወደዚህ ባር የመጣሁት ራሴን ላጠፋ ነበር። አንተ ግን መርዜን ጠጣህብኝ።”

“የፅኑነት ሥሪት”

(ኄኖክ ስጦታው) 

(ሲያጣሙት ሚጣመም… ሲያቀኑት ሚቀና)
የቆመ ቢመስልም — ፍፃሜው ግን ገና።

ግትር ነው የሚባል — ላመነበት ፀንቶ
ፍፃሜው ላይ ቆሟል — መልመጥመጡን ረቶ።

የ"ፅኑነት'' ትርጉም― ለዚህ ዘመን ድርሻ
ለሟችም ለኗሪም…
አለመታመን ነው — መታመን እያሻ።

አምናለሁ

(ኄኖክ ስጦታው)

አምናለሁ፣
     አምናለሁ፣
              አምናለሁ፣  
                         አምናለሁ
(አምኜ እጥራለሁ)
ጥሬ፣ ጥሬ፣ ጥሬ ፦ እምነት እገነባለሁ።
ስጠረጥር ጊዜ፣ (ሁለት) እንዳለሁ!
ታጥሮ በእምነቴ፣ ንጄው የሚሰፋ
“አንዱ” ራሱ እምነት፣ ሌላኛው ነው “ተስፋ”።
ተስፋ እገነባለሁ፦ እምነት አንፃለሁ፦ ጥላቻን ጠልቼ
(ጥርጣሬን ንጄ፣ እምነትንም ንጄ፣ ሌላነትን ሽቼ)
ማፍረስም መስራት ነው፣ መስራትም ነው ማፍረስ፣ አምናለሁ ተግቼ።

2017 ጃንዋሪ 4, ረቡዕ

“በፍቅር ሥም” ለንባብ በቃ

የደራሲና ሃያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ አሥረኛ መጽሐፍ እና አምስተኛው ልቦለድ “በፍቅር ሥም” ለንባብ በቃ