2016 ኤፕሪል 22, ዓርብ

ፍተላ

(ኄኖክ ስጦታው ናኁሰናይ)

ከዕለታት ባንዱ ጠዋት ነው።
ሌሊቱን ኦቭረን ጠዋት ላይ ነዳጅ ልቀዳ ማደያ ውስጥ ገባሁ።

"የስንት ልቅዳልህ?" አለ ነዳጅ ቀጂው።

"ደብል ቅዳልኝ" በግማሽ ልብ ሆኜ ነበር የመለስኩለት።

"የምን ደብል?"

ግሮሰሪ እንዳልገባሁ ትዝ ሲለኝ ፦ "ፉል አድርገው። የሃምሳ ብር!" አልኩት።

በግርምትና በድንጋሬ ከላይ እስከታች አይቶኝ እንዲህ አለ፦

"ላይተር ነው የምታስሞላው?"