2016 ማርች 16, ረቡዕ

የችሎት *ዳ ኄኖክ ስጦታው ናኁሰናይ

የችሎት *ዳ
ኄኖክ ስጦታው ናኁሰናይ

ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
የተናገርኩት ቃል፣ ፍርድ ቤት ቀረበ
የክሱ ሙሉ ቃል፣ ይላል "ተሳደበ"¡
"ተ*ዳ"
*
ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
ታግሼው
ዝም ያልኩት ተዘሎ፣ ለችሎት ቀረበ
ሰምቶ ፈራጅ ዳኛ፣ ክሴን አነበበ…

"ተቃውሞ"

ዝም!

"ማቅለያ"

ዝም!

"አቤቱታ"

ዝም!

ዳኛው…
"ዝም ያለ ተከሳሽ፣ ወንጀሉን አመነ"፣ ብሎ አነበነበ
ይሄኔ ተናገርኩ፣ ቃሌ ተከተበ

"ከፍድ በፊትና ከመክሰስ ቀድሞ፣ ማነው የታቀበ?!
ትእግስት ያለው ማነው፣ ከዚህ ክሴ ቀድሞ፣ ዝም እንዳልኩ ያሰበ?!"
*

ችሎት ተ-----!