2012 ዲሴምበር 31, ሰኞ

ከሞተች ቆይቷል


ሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ

ከሞተች ቆይቷል ብዙ ዘመን ሁኑዋል
ብዙ ነበር ጊዜው
ግን ፎቶግራፍዋ፣ ደብዳቤዋም አለ
በጠጉርዋ ጉንጉን የጠቀለለችው
ምን ቀነ ቀጠሮ ነው
ቀን የቀን ጎደሎ
የቀን ጥቁር መጥፎ፡፡
አበባ ሄድኩ ይዤ …
እዚያ አበባ አልጠፋም
በመቃብርዋ ውስጥ አበባ ተኝትዋል፡፡
ስሜቴ ፈነዳ ገላዬን በተነው
ነፍሴን ነቀነቃት
እንባዬ ወረደ ጉንጬን አረጠበው
ለተረሳ ነገር እንዴት ያለቅሳል ሰው!
ለተረሳ ነገር
ምን ጊዜው ቢረዝም . . .
የዚህ አለም ጣጣ እንከራተተኝ
የዚህ አለም ስቃይ እየቦረቦረኝ -
ሲጨንቀኝ ሰውነት
ፍቅሬ ይሁን ያንቺ የኔ መቃብር ቤት፤
ህይወት ነዶ ጠፍቶ ሞት ፍሙን ሲያዳፍን
ያን ጨለማ ጉዋዳ ሄጄ ልተኛበት፡፡
ይመስላል ዘላለም . . .

2012 ዲሴምበር 30, እሑድ

“ትጠምቂልኝ ጀመር”



“ትጠምቂልኝ ጀመር”
ለጠላሽ መጥመቂያ፣ ጋኑን አጥነሻል
ብቅል አብቅለሻል፣ አሻሮ ቆልተሸል
ጌሾ ቀንጥሰሻል፣ እንኩሮ አንኩረሻል…
* * *
ተጠጥቶ ሳያልቅ፣ ከጋን ያለው ጠላ
ቅራሪው ሳይወጣ፣ ትጠምቂያለሽ ሌላ፡፡
* * *
ያን ሰሞን ሳልጠጣ
በፍቅርሽ ሰክሬ፣ ስምሽን ክንዴ ላይ-
በመርፌ ስነቀስ
በምናብ ስቃትት፣ በቅናት ስጠበስ
አንቺም አትጠምቂ፣ እኔም ጠላ አልቀምስ፡፡
የፍቅራችን እድሜ፣ በጨመረ ቁጥር
የጎሸ - ያልጎሸ፣ አንዳንዴም ፍሊተር
ጠላ በየአይነቱ፣ ትጠምቂልኝ ጀመር፡፡
ሄኖክ ስጦታው
 

2012 ዲሴምበር 27, ሐሙስ

“The Prophet” by Khalil Gibran~On Marriage, On Children, On Giving


The Prophet free ebook by Khalil Gibran Public Domain PDF
Download “The Prophet” 
by Khalil Gibran in ebook
 It was written in English by the Lebanese Khalil Gibran and published in 1923. Its poetic wisdom and the spiritual universal message has made it a modern classic now translated to more than 40 languages. The work is now in the Public Domain and can be downloaded here in full length as a PDF-file for free. We also have a public domain version ofThe Madman by Kahlil Gibran, you can find it here:

  • On Marriage
  • On Children
  • On Giving

On Marriage

      Then Almitra spoke again and said, "And what of Marriage, master?" 

      And he answered saying: 

      You were born together, and together you shall be forevermore. 

      You shall be together when white wings of death scatter your days. 
      Aye, you shall be together even in the silent memory of God. 
      But let there be spaces in your togetherness, 
      And let the winds of the heavens dance between you. 
      Love one another but make not a bond of love: 
      Let it rather be a moving sea between the shores of your souls. 
      Fill each other's cup but drink not from one cup. 
      Give one another of your bread but eat not from the same loaf. 
      Sing and dance together and be joyous, but let each one of you be alone, 
      Even as the strings of a lute are alone though they quiver with the same music. 
      Give your hearts, but not into each other's keeping.
 
      For only the hand of Life can contain your hearts.
 
      And stand together, yet not too near together:
 
      For the pillars of the temple stand apart,
 
      And the oak tree and the cypress grow not in each other's shadow.
 


On Children
      And a woman who held a babe against her bosom said, "Speak to us of Children." And he said: 
      Your children are not your children.
 
      They are the sons and daughters of Life's longing for itself.
 
      They come through you but not from you,
 


      And though they are with you, yet they belong not to you.
 
      You may give them your love but not your thoughts.
 
      For they have their own thoughts.
 
      You may house their bodies but not their souls,
 
      For their souls dwell in the house of tomorrow, which you cannot visit, not even in your dreams.
 
      You may strive to be like them, but seek not to make them like you.
 
      For life goes not backward nor tarries with yesterday.
 
      You are the bows from which your children as living arrows are sent forth.
 

      The archer sees the mark upon the path of the infinite, and He bends you with His might that His arrows   
      may go swift and far. 
      Let your bending in the archer's hand be for gladness; 
      For even as he loves the arrow that flies, so He loves also the bow that is stable.
 



The Prophet by Khalil Gibran-The Coming of the Ship and On Love


Download
 “The Prophet” by 
Khalil Gibran in ebook
   It was written in English by the Lebanese Khalil Gibran and published in 1923. Its poetic wisdom and the spiritual universal message has made it a 

modern classic now translated to more than 40 languages. The work is now in the Public Domain and can be downloaded here in full length as a PDF-file for free. We also have a public domain version of The Madman by Kahlil Gibran, you can find it here:
  • The Coming of the Ship
  • On Love

The Prophet free ebook by Khalil Gibran Public Domain PDF
The Coming of the Ship
      Almustafa, the chosen and the beloved, who was a dawn unto his own day, had waited twelve years in the city of Orphalese for his ship that was to return and bear him back to the isle of his birth. 
      And in the twelfth year, on the seventh day of Ielool, the month of reaping, he climbed the hill without the city walls and looked seaward; and he beheld the ship coming with the mist.
 
      Then the gates of his heart were flung open, and his joy flew far over the sea. And he closed his eyes and prayed in the silences of his soul.
 

2012 ዲሴምበር 16, እሑድ

የአክሱም ጫፍ አቁማዳ ~ ደበበ ሰይፉ


ገጣሚ ፣ ጸሐፊ ተውኔትና የሥነጽሑፍ ተመራማሪ ደበበ ሰይፉ















የአክሱም ጫፍ አቁማዳ PDF
/ደበበ ሰይፉ/

ትግራይ ላከ ወሎ ጋ አበድሮኝ ብሎ አንድ ቁና ጤፍ
ወሎም አፈረና የለኝም ማለቱን ባህሉን መዝለፍ
            ቆሌውን መንቀፍ
ላከ ወደሸዋ ምናልባት ቢሰጠው ለሰው እሚተርፍ።
ሸዋም አፈረና የለኝም ማለቱን ወደ ሐረር ዞረ
ሐረርም መልሶ ባሌን አተኮረ
ባሌም ወደአርሲ አርሲ ሲዳሞን
ሲዳሞም ተክዞ፣ ግን የለኝም ብልስ ማን ያምነኛል ብሎ
ወደ ጋሞ ላከ አቁማዳ ጠቅሎ።

ጋሞን ብርድ መታው ሐዘን ገባውና
የራሱን ምንዳቤ የግል ስቅየቱን ችሎት በጥሞና
በጋቢ ጀቡኖ የልቡን ጠባሳ ሲኖር እንደ ደህና
ዛሬ የወንድሙን የእርዳኝ አቤቱታ መስማት አልቻለና።
አውጥቶና አውርዶ ላከ ወደ ከፋ እጅግ አስተዛዝኖ
ከሀፍረት ያድነኛል ከረሃብ ያወጣኛል ሲል በአያሌው አምኖ።

2012 ዲሴምበር 8, ቅዳሜ

ሃ ገ ሬ በ ገብረክርስቶስ ደስታ



ሃ ገ ሬ
{ሰአሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ}

አገሬ ውበት ነው፣

ለምለምና ነፋስ የሚጫወትበት፣

ፀሃይ የሞላበት፣ ቀለም የሞላበት።

አገሬ ቆላ ነው፣ ደጋ ወይና ደጋ፣

እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ እስኪነጋ።

አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ፣

አገሬ ጅረት ነው ገደልና ሜዳ፣

ውበት ነው በበጋ ፀሃይ አትፋጅም፣

ክረምቱም አይበርድም፣

አይበርድም፣ አይበርድም። 

አገሬ ጫካ ነው፣

እንሰሳት አራዊት የሚፈነጩበት፣

በወጥመድ ሳይገቡ ሳይነካቸው ጠላት።

እዚያ አለ ነፃነት፣

የቆጥ ላይ ቅስቀሳ 2


2012 ዲሴምበር 5, ረቡዕ

NILE: A Poem by Tsegaye Gebre-Medhin



I am the first Earth Mother of all fertility
I am the Source I am the Nile I am the African I am the beginning
O Arabia, how could you so conveniently have forgotten
While your breath still hangs upon the threads of my springs
O Egypt, you prodigal daughter born from my first love
I am your Queen of the endless fresh waters
Who rested my head upon the arms of Narmer Ka Menes
When we joined in one our Upper and Lower Lands to create you
bosom of my being
How could you so conveniently count down
In miserable billions of petty cubic yards
The eternal drops of my life giving Nile to you
Beginning long before the earth fell from the eye ball of heaven,
O Nile, that gush out from my breath of life
Upon the throats of the billions of the Earth's thirsty multitudes,
O World, how could you so conveniently have forgotten
That I, your first fountain, I your ever Ethiopia
I your first life still survive for you?

በሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ/ እኔ እወድሻለሁ


ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚሊዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንችን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ።
እኔ እወድሻለሁ
የሰማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ፅጌ-ረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደ ሎሚ ሽታ፡፡
እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
እኔ እወድሻለሁ፣
አበባ እንዳየ ንብ፡፡

2012 ኖቬምበር 29, ሐሙስ

ፍቅር ጥላ ሲጥል በ-ገብረ ክርስቶስ ደስታ


ፍቅር ጥላ ሲጥል

በገና
ቢቃኙ፡
ሸክላ
ቢያዘፍኑ
ክራር
ቢጫወቱ፡
ለሚወዱት
ምነው
ሙዚቃ
ቢመቱ
ቢቀኙ
ቢያዜሙ
ቃል
ቢደረድሩ
ጌጥ
ውበት
ቢፈጥሩ
ቤት
ንብረት
ቢሠሩ
አበባ
ቢልኩ
ደብዳቤ
ቢልኩ
ምነው ______
ቢናፍቁ !
አገር
ቢያቋርጡ ______
ቢሔዱ
ቢርቁ
ዓመት
ቢጠብቁ
ዘመን
ቢጠብቁ።
ለሚወዱት ምነው ....

ገብረ ክርስቶስ ደስታ

1998 96-97


Tsegaye Gebre-Medhin Ethiopia's poet and playwright of the common people


The poet and dramatist Tsegaye Gebre-Medhin, who has died aged 69, was considered Ethiopia's poet laureate. He was one of the most important literary figures that country has produced in the last hundred years, and certainly the best known, both within and outside it; his 1960s decision to write about the common man, rather than religion and royalty, marked the beginning of modern Ethiopian theatre. He wrote in English and was a translator of Shakespeare, but his real gift and achievement was to harness the considerable lyrical powers of his own, Ethiopian, languages.
This was often achieved under trying circumstances. His career spanned three regimes: Emperor Haile Selassie I's feudal rule, Mengistu Hailemariam's Marxist dictatorship (under which he was briefly imprisoned), and the putative democracy of Meles Zenawi. All three banned his plays; he once estimated that of 49 works, 36 had at one time or another been censored.
Tsegaye was born in Boda, a village some 120km from the capital, to an Oromo father, who was away fighting the Italians, and an Amhara mother. (The two groups speak languages from entirely different linguistic groups, Cushitic and Semitic respectively; the latter has an alphabet of some 300 letters.) As many Ethiopian boys do, he also learned Ge'ez, the ancient language of the church, an Ethiopian equivalent to Latin; he also helped the family by caring for cattle. He was more unusual in beginning to write plays when at the local elementary school. At 16 he transferred to the Wingate school in Addis Ababa, where he developed an interest in pantomime; this was followed, in 1959, by a degree from the Blackstone School of Law in Chicago. He had not forgotten his first love, however; the following year he used a UNESCO scholarship to do an educational tour that included visits to the Royal Court Theatre in London and the Comédie Française, Paris.

The 1960s were an important decade. He returned to Ethiopia in 1960 to run the Municipality Company at the National Theatre and establish a school which produced a number of leading Ethiopian actors. Realising the usefulness of Shakespeare in the making of dangerous political points, he translated Macbeth and King Lear. He also translated Molière's Tartuffe, and wrote a play in English called Oda Oak Oracle, which was performed in theatres in Ethiopia, Britain, Denmark, Italy, Romania, Nigeria, Tanzania and the US, and still appears on reading lists in black studies departments. But it was Yekermew Sew (Tomorrow's Man) which established his place in Ethiopian theatre."Drawing from Ge'ez and Amharic and Orominya, he was able to coin phrases which, in normal Amharic language, don't exist, but are powerful and expressive," says Tamrat Gebeyehu, author of the Ethiopian entry in the World Encyclopedia of Contemporary Theatre. Thus it was "a pleasure to hear his characters talk, even though chances were you did not understand 50% of what they were saying." In 1966, aged 29, he became the youngest person ever to receive the Haile Selassie I Prize for Amharic Literature.
Briefly, he was appointed minister of culture, but Haile Selassie was deposed by Mengistu Hailemariam and, during the Red Terror in 1975, Tsegaye and the playwright Ayalneh Mulatu spent months together in a prison cell. Ayalneh, who remained friends with Tsegaye for the rest of his life, remembers a daily 11am roll call of men to be killed, and the day his own name came up. It was mispronounced, and Tsegaye seized on the mispronunciation to argue they had the wrong man, thus saving Ayalneh's life. They wrote poems and plays on the paper bags their food came in.
Agit-prop came into its own under the Marxist regime, as did Tsegaye's own brand of declamatory nationalism. He wrote Inat Alem Tenu (or Mother Cour- age, though he borrowed only the title) and Ha Hu be Sidist Wer (ABC in Six Months), which referred to the period of the emperor's deposition. In 1979 he helped to establish the theatre arts department at Addis Ababa University where he is remembered as being very strict and aloof. In the 1980s he also wrote historical plays about Ethiopian kings, one of which, Tewodros, was performed at the Arts Theatre in London in 1986. In 1993, after Mengistu Hailemariam was in turn deposed, he wrote a companion piece to Ha Hu be Sidist Wer. This was Ha Hu Weynis Pe Pu - A or Z, a play about peace, which the current regime banned.
There are persistent reports that the actors were beaten while on tour. Despite this, "I like to go out and communicate with the common folk of Ethiopia," Tsegaye wrote in 1999. "The peasant, the patriot, the soldier, the traitor, the housewife, the priest, the sheikh ... It is from them that I learn about my country and people. And generally their comments are accompanied by tears; their stories are mostly melancholy; their memories are bitter and tragic. It is that which I reflect in my writings. That is why my plays dwell on tragedy."
In 1998 he moved to New York to undergo dialysis, virtually unavailable in Ethiopia, and to be near his children. He remained active, promoting Ethiopian culture, until the end. In 2002 the African Union took one of his poems as its anthem. He is survived by his wife Lakech Bitew, three daughters, Yodit, Mahlet and Adey, and three sons, Ayenew, Estifanos and Hailu. Tsegaye Gebre-Medhin, poet and dramatist, born August 17 1936; died February 25 2006 http://www.guardian.co.uk/news/2006/may/03/guardianobituaries.booksobituaries

2012 ኖቬምበር 16, ዓርብ

ወና ልብ; የትዕግስት ዓለምነህ ግጥም


ወና ልብ
ከልቧ ሜዳ ላይ፤
ፀሐይ ወጥታ ብታይ፤
ባልታጠረ ግቢ፣ ባላስከበረችው፤
ቅጥር በሌለው ደጅ፣ ወና በተወችው፤
ውሃ እንዲያነሳላት፣ ቢከረክር ወዳ፤
ስንዴዋን አስጥታ፣ ወደ መንደር ሄዳ፤
ቤቷ ላይጨስበት፣ ላትጐልት ጉልቻ፤
ንፍሮም ላትቀቅል፣ ላትጋግር እንጐቻ፤
"እሽ..." ባልተባሉ፣ ዶሮዎች ተለቅሞ፤
አጋች በሌላቸው፣ እሪያዎች ተቅሞ፤
‘ባፋሽ ባጐንባሹ‘፣ እንዳልነበር ወድሞ፤

በጠበቃት ስጡ፣ ሰርክ ስትገናኝ፤
ከመጅ ከማሰሮ፣ በወግ ሳትሰናኝ፤
በዛለ ጉልበቷ፣ ብቻዋን አራግፋ፤
ከነግሳንግሱ፣ ዳውጃዋን አጥፋ፤
ቀኗ ሊመሽ ሲድህ፣ ስትገባ መጀቷ፤
ቆፈኑ ተሰማው የተራበ አንጀቷ፡፡

/ትዕግስት ዓለምነህ/
ጥቅምት 3 ቀን 2005 ዓ.ም.

እኔ’ና’ኔ


ይኼ ልቤ . . . አልታወቀ - ሔርሜላ ትጽፋለች!!


ይኼ ልቤ . . . አልታወቀ
መቼ አምልጦ እንደመጣ
መቼስ አመል እንዳወጣ
ቤትህ ደርሶ - ደጅ አንኳኩቶ
ሳይታሰብ - አፀድህን ዘልቆ ገብቶ
ሳይጠራ - ከእልፍኝህ ተሰይሞ
ሳይጋበዝ - ከማዕድህ ታድሞ
ሳይታይ - አብሮህ ከዋለ ካደረ
እኔን ትቶ ካንተ መኖር ከጀመረ
ሰ - ነ - በ - ተ
ግና . . . ተግባር እንደል'ም አልቀለለ
እግሬ ልቤን መች ተከተለ
ከደሳሳ ጎጆዬ በራፍ ቆሜ (በሙሉ ዓይኔ እንኳ ሳልደፍር)
የኮራ አፀድህን ሳይ አግድሜ
ዓይኖቼ ሊያዩህ እንደናፈቁ
ጣቶችህ ከእጆቼ እንደ'ልም እንደራቁ
ምን አለብህ . . . በኮራ የንጉስ ርምጃህ
በመንደሩ ተንጎማልለህ
የኔ እግር ብርክ ሳይታይህ
እንደዋዛ ታልፈኛለህ . . .
ባለሹመት አጀበ ብዙ
ገደብ የለሽ ዓለም ደርዙ
ቢያነቅፍህ 'ልነጠፍ' ባይ የማታጣ
መካችህ ብዙ ቢያጋጥምህ የሚቃጣ
እና ለምን . . . እንዴት ተብሎ
ዓይንህ ወደኔ 'ሚያይ አሽቆልቁሎ
ቊንዳላህ ቢፈተሸ - ቢመረመር ቆዳህ
የቆነጃጅት ቃል - ድሪ ጌጣጌጥህ
ዓይናቸው መዋያህ - ልባቸው ማደሪያህ
ታዲያ ማን ከአጀቡ ነጥሎ
ከዙሪያህ የዓይን አዋጁን አግልሎ
ያመላክትህ ክሳይ መልኬን
ባይንህ ያግባ ልጥፍ ዳሴን?
የኔን ዓለም ሞልተህ - መውጣትህ መንጋቱ
ሲሆንልኝ ኖረ - መግባትህ መምሸቱ
ባታስተውለኝም በዓለምህ ባልታይ
ከቤቴም ባይሞላ አዱኛ ወ ሲሳይ
ይህንን አውቃለሁ . . .
ንጉስ ከእረኚት ጋር - በፍቅር ወደቀ
መደምደሚያው ሆና - ሌላ ውበት ናቀ
ስለዚህ . . . እንዲህ ነው ጸሎቴ
ባጠገቤ ስታልፍ አንድ ናት መሻቴ
እንቅፋት በመታህ - በጣለህ ከእርሻዬ
ክፉኛ አንሸራቶህ - ውደቅ ከማሳዬ
ላንዲት ደቂቃ እንኳ - መኖሬን እንድታውቅ
ቁስልህን ለማከም - ኖራለሁ ስናፍቅ
June 2011


Hermy Writes

2012 ኖቬምበር 8, ሐሙስ

ጥቂት ፍልስፍና ከ (ዘገብረየሱስ)


ጥቂት ፍልስፍና
ቅዱስ መፀሐፍ ፣ ፈጣሪ ለ አዳም አጋር ትሆነው ዘንድ ሔዋንን ሲፈጥርልት ፣ አዳምን በከባድ እንቅልፍ ጥሎት ነው ብሎ ያስተምራል። ዛድያ እኔ ደግሞ ትንሽ ተመራመርኩ። የ አዳም ከባድ እንቅልፍ ፣ ምን ይሆን ብዬ? ተያ ተመራምሬ ሳበቃ ፣ የ አዳም እንቅልፍ ለኔ ምነው ብዬ ራሴን ጠየቅኩት? ጠይቄም ፣ መልስ አገኘሁ። እንዲህ የሚል። አዳም ከእንቅልፍ ነቃ ፣ ሄዋንንም ከጎኑ አገኘ ፣ አጋርም ሆነቸው እናም ኑሮን አብረው ኖሩ። አብረው ተደስቱ ተዋረዱ ። ወልዱ ከበዱ። አብረውም ከፈጣሪ ምህረት አገኙ( እዚህ ላይ ግን ፣ ለ አዳም ቃል ገባለት እንጂ ፣ ስለ ሔዋን የተጠቀሰ ነገር ትዝ አይለኝም። ግን አንድም ሆነው የለም ፣ የአዳም የሆነው ፣ የሄዋን ነው ፣ የሔዋንም የ አዳም)። ወደኔ መለስኳት። የኔ እንቅልፍ አልኩኝ ፣ በልጅነቴ የኖርኩት እድሜ ነው። ወላጆች እንቅፋት እንዳይመታኝ ፣ እንዳይርበኝ እንዳይጠማኝ ፣ ሲያሳድጉኝ ፣ ያሳለፍኩት እድሜ። እናም ከዛ የእንቅልፍ እድሜ ስነቃ ፣ እና አይኖቼን ስገልጥ ፣ መጀመርያ ፣ የየኋትን ሔዋን ፣ ሔዋኔ ነች ብዬ አልኩ። እዚህ ላይ ፣ እንዴት አወቅክ ካላችሁ ፣ አዳምም ምርጫ አልነበርዉም። ከጎኑ ያገኛትን ተቀበለ እንጂ። እኔም እንደዛው። ከዛ ጥቂት መስመር ፣ ግጥም ሞነጨርኩኝ። እነሆ ጀባ ፣ (ይህ የኔ ፍልስፍና እንጂ ፣ የማንም አስተምህሮ አይደለም ፣ ስለጥቅ ደግሞ ፣ እኔ ግጥሜን ለማስደገፍ የተጠቀምኩት ፣ ሚዛን ነው ልበል ፣ እንጃ )
*ሔዋን*
ለብቻህ ስትኖር ፣
...........ሌቱን ስትገፋ
............ከምትርቅህ ተስፋ
ብሎ አስተዉሎ
........አጋር ለኔው ሰራ
እኔን በእንቅልፍ ጥሎ
..................ከአካሌ ከፍሎ
አፈጣጠርሽን ሳላዬው ቀርቼ
ጌታዬ ሲሰራሽ ፣ እንቅልፌን ተኝቼ
ድንገት ዛሬ ነግቶ ፣ ከእንቅልፌ ስንቃ
አጋር ጎን አጥንቴን ፣ ባያት ጎኔ ወድቃ
አፍ ፈታሁ በስሟ ፣ ገፅዋ ፊደል ሆኖ
ፍቅር ተማርኩ ከልቧ ፣ ልቤ ለርሷ መንኖ
እሱም አያስተኛኝ ፣ እኔን በእንቅልፍ ጥሎ
ሌላ አጋር አይስራ ፣ ከጎኔ ገንጥሎ
አንች ነሽ ብያለሁ ፣ የጎኔ ጎዶሎ

(ዘገብረየሱስ ጥቅምት 20-2005)

ጠብታ ቋጠሮ ፤ የሔርሜላ ግጥም


2012 ኖቬምበር 4, እሑድ

አባ ይፍቱኝ

ምን ተሰማዎት? አስተያየትዎ ይጠቅመኛልና ሃሳብዎን ይንገሩኝ

The Broken Wings






The Broken Wings . pdf
Kahlil Gibran 





FOREWORD
I was eighteen years of age when love opened my eyes with its magic rays and touched my spirit for the first
time with its fiery fingers, and Selma Karamy was the first woman who awakened my spirit with her beauty
and led me into the garden of high affection, where days pass like dreams and nights like weddings.
Selma Karamy was the one who taught me to worship beauty by the example of her own beauty and revealed

2012 ኦክቶበር 28, እሑድ

"የኢትዮጵያ ግጥም ፈርጥ" ለአጼ ይስሓቅ በዘመኑ ከተገጠመላቸው የተወሰደ


ዓፄ ይስሐቅ




ቀዳማዊ አጼ ይሥሓቅ በዙፋን ስማቸው "ዳግማዊ ገብረ መስቀል" ሲባሉ እ.ኤ.አ ከ1414-1429 የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የነበሩ ናቸው። የቀዳማዊ አጼ ዳዊት ሁለተኛ ወንድ ልጅ ሲሆኑ የቀዳማዊ ቴዎድሮስ ታናሽ ወንድም ናቸው።

በግብጽ ቆብጦች ላይ በሚካሄድው ዘመቻ ምክናያት ብዙ ኮብቶች ወደኢትዮጵያ በዚሁ ዘመን ተሰደዱ። ከነዚህ ውስጥ ፋቅር አል-ዳዋ የተሰኘው የግብጹ ማምሉክ ባለሟል ይገኝበታል። ይህ ባለሟል በይስሓቅ ግዛት ውስጥ ተሰሚነት በማግኘቱ የአገሪቱን የግብር ስርዓት በመለወጥ በግብጽ ማምሉኮች በሚሰራበት መልኩ እንዲሆን አድርጓል። የንጉሱንም አለባበስ በመቀየርና መስቀል እንዲይዝ በማድረግ ንጉሱ ከቀሪው ህዝብ ለየተ እንዲል አድርጓል። በኋላም በራሳቸው በግብጽ እስላሞች መካከል በተነሳ ጠብ የቁስክፍለ ሃገር ገዢ የነበርው አሚር አል-ቱንቡጋ አል-ሙፍሪቅ በአጼ ይስሓቅ መንግስት ባለሟልነትን አግኝቶ በኋላ የንጉሱ ሰራዊት እንዲሻሻል አድርጓል። ይህ ግብጻዊ ለኢትዮጵያው ሰራዊት ካስተዋወቃቸው ነገሮች ውስጥ የእሳት ችቦ መወርወሪያ ዘዴንና የሻሞላ ውጊያን ይይዛሉ። እንደ ታሪክ አጥኝው ጅ.ቢ.ኸንቲንግፎርድ አባባል ከሆነ የኢትዮጵይ ነገስታት ቋሚ ዋና ከተማ ማድረግ ያቆሙት በዚሁ ንጉስ ዘመን ነበር።

2012 ኦክቶበር 17, ረቡዕ

የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች


ሼህ ሁሴን ጅብሪል

በሙሉ ግጥሙን ለመመልከት [PDF]
ሼህ ሁሴን ጅብሪል በወሎ አካባቢ በአፈታሪክ በስፋት የሚታወቁ ሼህ ናቸዉ። የተወለዱት በወሎ ክፍለ ሀገር በወረሄመኖ አውራጃ፣ በባዙራ ምክትል፣ በባሆች ቀበሌ፣ ልዩ ስሙ እምበለ ሴዳ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በ1811 ዓ.ም ገደማ እንደነበርና 1908 ዓ.ም በተወለዱ በ97 ዓመታቸው ማረፋቸዉ ይነገራል።

ሼህ ሁሴን ጅብሪል መፍረድ የጀመሩት ገና በሰባት ዓመታቸው እንደነበርና የሚናገሩትም መሬት ጠብ የማይል እንደነበር ይነገርላቸዋል። አሐዱ ወይም ቢስሚላሂ ብለው ፍርድ የጀመሩት ደግሞ በአጼ ዮሐንስና መምሬ ግርማ በተባሉ ቄስ ነበር ይባላል። የሗላ ሗላ ግን ወደፊት የሚሆነውንና የሚመጣውን ከነመፍትሔው ጭምር በግጥም ይተነብዩ እንደነበርና በዚህም ምክንያት ነገሥታቱም፣ መሳፍንቱም፣ ትንሹም ትልቁም እሳቸውን መጀን ማለት እንደጀመሩ ይነገራል። ምንም እንኳን በዚህ ፅሁፍ ዉስጥ ያካተትኳቸዉ ግጥሞች የሼህ ሁሴን ጅብሪል የራሳቸው ትንቢቶች ይሁኑ አይሁኑ የራሱ የሆነ ጥናትና ምርምር የሚያስፈልገዉ ጉዳይ ቢሆንም፣ ሼህ ሁሴን ጅብሪል ግን በትንቢታዊ ግጥሞቻቸዉ ከአጼ ዮሐንስ አራተኛ ጀምሮ እስከ ወታደራዊ ደርግ አገዛዝ መጨረሻ፥ ምናልባትም አሁን እስካለንበት ኢሕአዴግ ዘመን ድረስ ያለውን የኢትዮጵያ ታሪክ ቀድመዉ እንደተነበዩና በግጥም እንዳስቀመጡ በአፈታሪከ ይነገርላቸዋል።

ከአጼ ቴዎድሮስ፣ አጼ ዮሐንስ፥ አጼ ምኒልክ፥ እቴጌ ጣይቱ፥ ልጅ ኢያሱ፥ ንግሥት ዘውዲቱ፥ ተፈሪ፣ አጼ ኃይለ ሥላሴ፣ ደርግ፣ ወዘተ ጋር የተያያዙ ብዙ በርካታ ጉዳዮችም በስፋት በግጥሞቻቸዉ ዉስጥ ተነሰተዋል። ሼህ ሁሴን ጅብሪል አፄ ሚኒሊክ አድዋ ላይ ከጣሊያን ጋር እንደሚዋጉና በጦርነቱም ድል እንደሚቀናቸዉ ቀድመዉ ተንብየዋል፡ ከአድዋ ጦርነትም በሁዋላ ጣሊያን ተመልሶ ኢትዮጵያን እንደሚወርና ከአምስታመት ቆይታ በሁዋላ ተመልሶ ከሀገር እንደሚባረር፣ ሆኖም በነዚህ የአምስት አመታት የቆይታ ጊዜ ዉስጥ ብዙ ሰዉ በግፍ እንደሚገደል ጭምር ተንብዬዉ እንደነበር ይነገራል። ለምሳሌ ያክልም፣ የጽሑፍ ጥናት ገና ያልተጠናቀቀ ቢሆንም፣ የሼህ ሁሴንን ትንቢታዊ ግጥሞች ለማጥናትና ለማነጻጸር፣ ለሚፈልጉ ምሁራንና ተማሪዎች ይረዳል ብለዉ በማሰብ ዶ /ር ጌቴ ገላዬ 1996 ዓ.ም በእጅ ተጽፎ ፎቶ ኮፒ ከተደረገ አንድ አነስተኛ ደብተር አግኝተዉ ካጠናቀሩትና በኢንተርኔት እንዲሰራጭ ካደረጉት ብዛት ያላቸዉን የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞችን ካተተ መጣጥፋቸዉ ዉስጥ ከዚህ የሚከተሉት ሁለት ግጥሞች መዉሰድ ይቻላል።
ሥራቸው ባለጌ አህያ የሚበሉ
ባሕር ወዲያ ማዶ ክፉ ሰዎች አሉ፣
ሐበሻን ለመውረር ሐሳብ ያስባሉ
የኋላ የኋላ መምጣት ይመጣሉ
አምስት ዓመት ገዝተው ወዲያው ይሄዳሉ።
ድንጋይ ዱቄት አርገው መንገድ የሚያበጁ
ገመድን ዘርግተው መብራት የሚያበጁ
አህያ የሚያርዱ አሞራ የሚፈጁ
መጡ እየተማሩ ሐበሻን ሊያበጁ
ማማሩን አማረች ግን ብዙ ሰው ፈጁ።
ስለ ወታደራዊ አገዛዝ የደርግ መንግስትና በጊዜዉ ስለ ነበረዉ የመሬትና ሹመት ጣጣ አስመልከተዉ ሼህ ሁሴን ጅብሪል በትንቢታዊ ግጥማቸዉ እንዲህ ብለዉ አስጠንቅቀዉ እንደነበርም ይነገራል።
በሰማይ ቀበሌ መላኢሞች ሲያወጉ
በአጼ መባል ቀርቶ ይባላል በደርጉ
ያን ጊዜ በዱአ እንዳትዘነጉ
መሬትና ሹመት እንዳትፈልጉ።

2012 ኦክቶበር 9, ማክሰኞ

ለፈጠራት ፀፀት / የትዕግስት ዓለምነህ ግጥም


ለፈጠራት ፀፀት
በሚርመሰመሰው፣ የጥምቀት ታዳሚ፤
የሻሞ እንደሚሏት፣ እንደጣሏት ሎሚ፤
እንደመያዝ ያህል፣ እድል ለሷ ጠባ፣
አይታ ትቀራለች፣ እምነትና ተድላ፤
አለም ግሳንግሷን፣ በእሷው ላይ ቆልላ፡፡
ፍቅሯ እንደ ትልቅ ወንዝ፣ ቢሆንም ፍጥረቷ፤
ገባሮቿ አቅመ ቢስ፣ ሆነው ለህይወቷ፤
መች ሲሻገር አየች፣ ኩራቱ ከመኸር፤
በጋው ሲያብት ጠፋ፣ እንኳን ሊገማሸር፡፡

2012 ኦክቶበር 1, ሰኞ

ሞክሼ የአማርኛ ፊደላት እና የባለሙያዎች ማብራሪያ ክፍል ሁለት


ሞክሼ የአማርኛ ፊደላት

እና

የባለሙያዎች ማብራሪያ

ክፍል ሁለት




የሄኖክ ስብስብ(henoksitotaw65@gmail.com)


ታህሳስ 2005ዓ.ም

ውድ አንባቢዎች፤ ከዚህ በታች የምታነቡት ሀሳብ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ላይ የተነበቡ ሲሆን ምንጫቸውም ከየመጣጥፎቹ ግርጌ ይገኛል፡፡ ለዚህም ነው “ስብስብ” በሚል ለመግለፅ የተገደድኩት፡፡ በስብስብ መጣጥፎቹ ላይ የጨመርኩት አንዳች ነገር የለም፤ ምክንያቱም አላማዬ በሞክሼ ፊደላት እና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ለመበየን ሳይሆን፣ እንደኔው ግራ ለተጋቡት ማጋራት ነውና፡፡


-5-

በዲ/ን ኅሩይ ባየ

   . . .ኢትዮጵያ ከምትታወቅባቸው ዐበይት ሀብቶቿ ውስጥ አንዱ የራሷ የሆነ ፊደልና ቋንቋ እየተጠቀመች ለትውልድ ስታስተምር መኖሯ ነው፡፡ ለዚህም የፊደል፣ የቋንቋ ዕድገትና ሥልጣኔ ከፍተኛውን ድርሻ የምትይዘውና በር ከፋቿ የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ዛሬም እንደ ጥንቱ የሆሄያቱ ታሪክ እንዳይረሳ መልክአቸው እንዳይጠፉ ለትውልዱ ታስተምራለች፡፡ ስለሆነም በዘንድሮው የመስቀል በዓል በመስቀል ዐደባባይ አራቱ ሆሄያት እንዳይረሱ ትኩረት እንደሚያሻቸው ጥሪ ቀርቧል፡፡

ሆሄ የሚለውን ቃል ፊደል ተብሎ ሲነገር እንሰማለን፤ በጽሑፍም እናነባለን፡፡ ፊደልን ፈደለ ጻፈ ካለው የግእዝ ግስ አውጥተን ጽሑፍ የሚለውን ትርጉም እናገኛለን፡፡ በሌላ አተረጓጐም ፊደል የሚለው ግስ ጠብቆ ሲነበብ ፈጠረ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ ፊደል ፈጣሪ /መፍጠሪያ/ መባሉም ቃላትን ስለሚያስገኝ ነው፡፡ አባቶቻችን “ዘእንበለ ፊደል ኢይትነገር ወንጌል.. ያለፊደል ወንጌል አትተረጐምም” ማለታቸው ለመጻፍም ሆነ ለማንበብ፤ ለመተርጐምም ሆነ ለማመስጠር ፊደላት ጉልሕ ድርሻ እንዳላቸው ሲያመለክቱ ነው፡፡

2012 ሴፕቴምበር 30, እሑድ

ሞክሼ የአማርኛ ፊደላት እና የባለሙያዎች ማብራሪያ ክፍል አንድ


ሞክሼ የአማርኛ ፊደላት
እና
የባለሙያዎች ማብራሪያ

ክፍል አንድ

የሄኖክ ስብስብ
ታህሳስ 2005ዓ.ም
{PDF}
ውድ አንባቢዎች፤ ከዚህ በታች የምታነቡት ሀሳብ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ላይ የተነበቡ ሲሆን ምንጫቸውም ከየመጣጥፎቹ ግርጌ ይገኛል፡፡ ለዚህም ነው “ስብስብ” በሚል ለመግለፅ የተገደድኩት፡፡ በስብስብ መጣጥፎቹ ላይ የጨመርኩት አንዳች ነገር የለም፤ ምክንያቱም አላማዬ በሞክሼ ፊደላት እና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ለመበየን ሳይሆን፣ እንደኔው ግራ ለተጋቡት ማጋራት ነውና፡፡
-1-
የፊደል ዘር ይጠበቅ ባህሉም ይከበር
በፊታውራሪ አበበ ሥዩም ደስታ
በፊደሎቻችን ላይ ሦስት ሀ - ሐ - ኀ፣ ሁለት አ - ዐ -፣ ሁለት ሠ - ሰ ሁለት፣ ጸ - ፀ አሉ፡፡ እነዚህ ፊደሎች የራሳቸው የሆነ የስም አጠራርም አላቸው፤ ሀሌታው ሀ፣ ሐመሩ ሐ፣ ብዙኃን ኀ፣ ንጉሡ ሠ፣ እሳቱ ሰ፣ ጸሎት ጸ፣ ፀሐዩ ፀ ይባላሉ፡፡ በጽሑፍ የሚገቡበትን ተገቢ (ተስማሚ) ቦታም አላቸው፡፡ ለምሳሌ በሁለት ፊደሎች መጠቀም ይቻላል፡፡ ሀገር አገር ይህ ትክክለኛ አጻጻፍ ሲሆን፤ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ሐገር፣ ኀገር ብሎ መጻፍ ግን ስሕተት ይሆናል፤ የሚከተሉትን ደግሞ እንመልከት፤

ሕገ መንግሥት፣ ሕገ ወጥ፣ ሕዝብ፣ ሕብረት፣ ዓቃቤ ሕግ፣ ወዘተ. የመሳሰሉት አጻጻፋቸው ትክክል ነው፡፡ ከዚህ ልማዳዊ አሠራር ውጪ ህገ መንግሥት፤ ህገወጥ፤ ህዝብ፤ ህብረት፤ አቃቤ ህግ ስሕተታዊ አጻጻፍ ይሆናል፤ ሌላ ማስረጃ ቢፈለግ፤ ኃይለሥላሴ የሚለው ስም ሦስት የተለያዩ ፊደሎች ይዟል፡፡ የመጀመርያው ፊደል ብዙኀን - ኃ - ሲሆን፣ ከንጉሡ -ሥ- ሳድስ፣ ከእሳቱ -ስ- ሃምስን በመጻፍ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ ሀይለ ስላሴ ብሎ ቢጻፍ ግን የፊደሎቻችን የአጻጻፍ ሥርዓት ማፋለስ ይሆናል፤ በአቦ ሰጡኝ ፊደሎቻችን አለቦታቸው መግባትም፣ መጻፍም የለባቸውም፡፡

በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በማስታወቂያ ሚኒስቴር ረዳት ሚኒስትር የነበሩት የተከበሩ ብላታ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ የቅድሚያ ዓይነተኛ ሥራቸው የፊደሎች ዘሮች አለቦታቸው እንዳይጻፉ መጠበቅ ነበር፤ በዚያን ወቅት ተማሪ ሁኜ አልፎ አልፎ በጋዜጣ እንዲወጣልኝ አንድ አንድ ሐሳብ በማመንጨት እጽፍ ስለነበር ብዙ ጊዜ አርመውኛል፡፡

ከእሳቸው በተማርኩት ትምህርትና ባገኘሁት ልምድ አእምሮዬን አሻሽያለሁ፡፡ በቀድሞው የንጉሠ ነገሥቱ ዘመነ ሥርዓት የክፍል ሹም የመጀመርያ ሹመት ሆኖ ወደ ላይ እንደሚከተለው ይዘልቃል፡፡ ዲሬክተር ዋና ዲሬክተር፤ ረዳት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር፣ ሚኒስትር ዲ-ኤታ፤ ሚኒስትር፡፡ ከምክትል ሚኒስትር ወደ ላይ ያሉት እስከ ሚኒስትር ማዕረግ የደረሱት ክቡር ይባላሉ፡፡ ከዚህ በታች ያሉትን ግን ክቡር አይባሉም፡፡ በተመሳሳይ ያሉትን ማለት ኮሚሽነሮች፤ ሌ/ጀኔራሎች፣ አምባሳደሮች ክቡር ይባላሉ፡፡ ሚኒስትሮች የነበሩ በዳሬክተርና በሥራ አስኪያጅነት ሥራ ቢመደቡ እንኳን የቀድሞውን የሚኒስትር ማዕረጋቸውና ክብራቸው አይቀነስባቸውም፡፡ ክቡር መባል አለባቸው፡፡ ሥርዓት ነውና፡፡ ይህንኑ መለመድ ይገባዋል፤ በወታደሩ ሹመት አሰጣጥ ግን ያለው ሥርዓት የተጠበቀ ስለሆነ መልካም ነው እላለሁ፡፡ ከዚሁ ሌላ የምለው አለኝ፡፡ ባሁኑ በኢሕአዴግ መንግሥት ዘመን አምባሳደር ነዋሪ የማዕረግ መጠሪያ ስም ሆኖአል፡፡ አንድ አምባሳደር የዲፕሎማሲውን ሥራ አቁሞ ሲዛወር ልክ በሥራው እንዳለ ተቆጥሮ “አምባሳደር” እየተባለ መጠራት የለበትም፡፡

ለምሳሌ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት አምባሳደርነት ተሹመው የነበሩት ክቡር አቶ ጋሻው ዘለቀ፣ ክቡር አቶ ዘነበ ኃይለ፣ ክቡር ልጅ መንበረ ያየህ ይራድ፤ ክቡር ፊታውራሪ መሐመድ ሲራጅ ብዙ ዘመን በአምባሳደርነት ሲሠሩ ቆይተው ተልእኮዋቸውን ፈጽመው ወደ አገራቸው ሲመለሱ አምባሳደር የሚል ቀርቶ በቀድሞ ስማቸው አቶ ተብለው ነበር የሚጠሩት፤ ይህንኑ ጠይቆ ለማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ፊታውራሪ የነበሩትም፤ ፊታውራሪ ተብለው ይጠራሉ፡፡ ዘላቂ ሆኖ ከሰው ጋር ቅጽል የማዕረግ ስም ሆኖ የሚያገለግል ነው፡፡ በራሴ ምሳሌ ልውሰድ፤ ከግርማዊ ጃንሆይ በአዋጅ የተሰጠኝ የማዕረግ ስም ፊታውራሪ ነው፤ በዚህ ምድራዊው ዓለም እስካለሁ ድረስ የምጠራበት ሲሆን፣ ከሞትኩም በኋላ እጠራበታለሁ፡፡ እንዲሁም በንጉሠ ነገሥቱ መልካም ፈቃድ የሚሰጠው የሥልጣንና ማዕረግ ተዋረድ ባላምባራስ፣ ግራዝማች፣ ቀኛዝማች ፊታውራሪ፣ ደጀዝማች፣ ቢትወደድ፣ ራስ ቢትወደድ፣ ልዑል ራስ፣ አልጋ ወራሽ፣ ንጉሥ ንጉሠ ነገሥት ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ብላታ፣ ብላቴን ጌታ፣ ፀሐፊ ትዕዛዝ፣ ሊቀ መኳስ በሕይወት ሳሉ ይጠሩበታል፡፡ ከሞቱም በኋላ ስማቸውና ታሪካቸው በተነሣ ቁጥር ከመቃብር በላይ ሆኖ በማዕረጉ ስም ይጠሩበታል፡፡