ልጥፎችን በመለያ Tsegaye G/Medhin በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ Tsegaye G/Medhin በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ሰኞ 17 ጁን 2013
ዓርብ 3 ሜይ 2013
ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት /ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን/
ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት
/ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን/
------------
አዬ፣ ምነው እመ ብርሃን? ኢትዮጵያን ጨከንሽባት?
ምነው ቀኝሽን ረሳሻት?
እስከመቼ ድረስ እንዲህ፣ መቀነትሽን ታጠብቂባት?
ልቦናሽን ታዞሪባት?
ፈተናዋን፣ ሰቀቀኗን፣ ጣሯን ይበቃል ሳትያት?
አላንቺእኮ ማንም የላት….
አውሮጳ እንዲሁ ትናጋዋን፣ በፋሽስታዊ ነቀርሳ
ታርሳ፣ ተምሳ፣ በስብሳ
ሂትለራዊ እባጭ ጫንቃዋን፣ እንደኮረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ፣ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት
ሥልጡን፣ ብኩን፣ መፃጉዕ ናት፤ ….
እና ፈርቼ እንዳልባክን፣ ሲርቀኝ የኃይልሽ ውጋገን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ፣ በርታ በይኝ እመ ብርሃን
ቃል ኪዳኔን እንዳልረሳት፣ እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን፡፡
አዎን፣ ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ፣ ተፈትቶ እንዳይከዳት ሠጋሁ …
አዋጅ፣ የምሥራች ብዬ፣ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከእናቴ ማኅፀን አርፌ
ከአፈርዋ አጥንቴን ቀፍፌ
ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟ ወዜን ቀፍፌ
በሕፃ እግሬ ድሄባት፣ በህልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ፣ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩት እና ከጥጃ፣ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ፤
በጋው የእረኛ አደባባይ፣ ክረምት እንደወንዙ ፍሳሽ
በገጠር የደመና ዳስ፣ በገደል ሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅ እና ከሚዳቋ፣ ከዥግራ ጠረን ስተሸሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ፣ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር ሩጫ ስገጥም፣ ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከናዳ ጫፍ ሣር አጨዳ፣ ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎች ራት፣ ለማታቸው ትንሽ ድርቆሽ
ለግልገሌ ካውሬ ከለል
እማሳው ሥር ጎጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል፣ ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ፣ ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሣር ሲለመልም፣ ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከንበል ሲል፣ ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ፣ ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ፣ በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ …..
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመ ብርሃን እረሳሻት?
/ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን/
------------
አዬ፣ ምነው እመ ብርሃን? ኢትዮጵያን ጨከንሽባት?
ምነው ቀኝሽን ረሳሻት?
እስከመቼ ድረስ እንዲህ፣ መቀነትሽን ታጠብቂባት?
ልቦናሽን ታዞሪባት?
ፈተናዋን፣ ሰቀቀኗን፣ ጣሯን ይበቃል ሳትያት?
አላንቺእኮ ማንም የላት….
አውሮጳ እንዲሁ ትናጋዋን፣ በፋሽስታዊ ነቀርሳ
ታርሳ፣ ተምሳ፣ በስብሳ
ሂትለራዊ እባጭ ጫንቃዋን፣ እንደኮረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ፣ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት
ሥልጡን፣ ብኩን፣ መፃጉዕ ናት፤ ….
እና ፈርቼ እንዳልባክን፣ ሲርቀኝ የኃይልሽ ውጋገን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ፣ በርታ በይኝ እመ ብርሃን
ቃል ኪዳኔን እንዳልረሳት፣ እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን፡፡
አዎን፣ ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ፣ ተፈትቶ እንዳይከዳት ሠጋሁ …
አዋጅ፣ የምሥራች ብዬ፣ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከእናቴ ማኅፀን አርፌ
ከአፈርዋ አጥንቴን ቀፍፌ
ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟ ወዜን ቀፍፌ
በሕፃ እግሬ ድሄባት፣ በህልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ፣ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩት እና ከጥጃ፣ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ፤
በጋው የእረኛ አደባባይ፣ ክረምት እንደወንዙ ፍሳሽ
በገጠር የደመና ዳስ፣ በገደል ሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅ እና ከሚዳቋ፣ ከዥግራ ጠረን ስተሸሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ፣ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር ሩጫ ስገጥም፣ ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከናዳ ጫፍ ሣር አጨዳ፣ ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎች ራት፣ ለማታቸው ትንሽ ድርቆሽ
ለግልገሌ ካውሬ ከለል
እማሳው ሥር ጎጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል፣ ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ፣ ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሣር ሲለመልም፣ ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከንበል ሲል፣ ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ፣ ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ፣ በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ …..
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመ ብርሃን እረሳሻት?
እሑድ 24 ማርች 2013
“የሁለት የረሃብ ግጥሞች ረዥም ጉዞ”
ለፕሮፌሰር ሱራፍኤል ግርማ /
Professor Sourafel Girma
Professor of Industrial Economics
School of Economics
The University of Nottingham
Nottingham NG7 2RD
United Kingdom
------
የተሰኘውን ጥናት እንዳነበው ለላኩልኝ
ምስጋናዬ ባሉበት ይድረስዎ
ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ግጥም እንደፈርጥ የሚያበሩ ሥራዎቹን ትቶልን ቢያልፍም እኛ የጥበብ አድናቂዎች በሕይወት እስካለን የባለቅኔውን መልካም ሥራዎች ስናወድስ እና ስንመረምር እንኖራለን፡፡
“የሁለት የረሃብ ግጥሞች ረዥም ጉዞ” በሚል ርእስ የላኩልኝ መልዕክት ጠቃሚነቱ ለሌሎች መሰሎቼ እና የጥበብ አድናቂዎች ጠቃሚነቱን ከግምት በማስገባት የፒ.ዲ.ኤፍ ቅርጹን ሳይለቅ እንደላኩልኝ ላስነብበው ወደድኩ፡፡ በድጋሚ ምስጋናዬ ይድረስዎት!!
ሄኖክ ስጦታው
Professor of Industrial Economics
School of Economics
The University of Nottingham
Nottingham NG7 2RD
United Kingdom
------
“የሁለት የረሃብ ግጥሞች ረዥም ጉዞ”
የተሰኘውን ጥናት እንዳነበው ለላኩልኝ
ምስጋናዬ ባሉበት ይድረስዎ
ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ግጥም እንደፈርጥ የሚያበሩ ሥራዎቹን ትቶልን ቢያልፍም እኛ የጥበብ አድናቂዎች በሕይወት እስካለን የባለቅኔውን መልካም ሥራዎች ስናወድስ እና ስንመረምር እንኖራለን፡፡
“የሁለት የረሃብ ግጥሞች ረዥም ጉዞ” በሚል ርእስ የላኩልኝ መልዕክት ጠቃሚነቱ ለሌሎች መሰሎቼ እና የጥበብ አድናቂዎች ጠቃሚነቱን ከግምት በማስገባት የፒ.ዲ.ኤፍ ቅርጹን ሳይለቅ እንደላኩልኝ ላስነብበው ወደድኩ፡፡ በድጋሚ ምስጋናዬ ይድረስዎት!!
ሄኖክ ስጦታው
![]() |
| “የሁለት የረሃብ ግጥሞች ረዥም ጉዞ” |
ቅዳሜ 9 ማርች 2013
ረሃብ ስንት ቀን ይፈጃል?- ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
እሑድ 24 ፌብሩዋሪ 2013
እንዳይነግርህ አንዳች እውነት ! - ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
እንዳይነግርህ
አንዳች እውነት ! - ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
ደንስ ጎበዝ ! ደንስ
ጀግና
ክራቫትህን አውልቅና
ሃሳብህን ልቀቀውና
ኮትክን ሸሚዝክን ጣልና
ርገጥ ፣ ጨፍር ፣ ደንስ
ጀግና !
ያን የሙዚቃህን ናዳ
፣ የኮንትራባሱን መብረቅ
ልቀቀውና ይድብለቅለቅ
ምድር በሆይታ ይጥለቅለቅ
!
ምንም-ምንም እንዳታስብ
፣ ሁሉን-ሁሉን እንድትረሳ
ደንስ ! ካካታው ይነሳ
ጨፍር ፣ ወለሉ እስኪበሳ
....
ሃይ-ሃይ ! ዋይ !
ሃይ-ሃይ ! በልበት
የጃዝ ፋንፋር አንኳኳበት
ራስክን እንዳታስብበት
፤
ሆ ! በል እሪ ! በል
ምታበት
ፎክርበት ፣ አቅራራበት
አናፋበት ፣ ሸልልበት
የሲቃ ሳቅ አስካካበት
ሆያ-ሆዬ ! በል ጩኽበት
ኡኡታህ መንኮራኩርክን
፣ እስኪያሰጥመው አጓራበት
ጭንቅላትክን ግዘፍበት
፣ ውቀጥበት ፣ ውገርበት ፣ ....
ዝግ ብሎማ ያሰበ እንደሁ
፣ ይነግርሃል አንዳች እውነት !
-----------
ባለቅኔ
ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
እሑድ 10 ፌብሩዋሪ 2013
እውነት አሁን አንቺ እሷ ነሽ! ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
እውነት አሁን አንቺ እሷ ነሽ! ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ
ገብረ መድኅን
---------
እሷ ነኝ በዪኝ ግድ የለም!
. . . .
ሁሉ ላፍ አልተፈጠረም
ቢሉም አፍ አይለው የለም።
ልወቀውና ላውጣ እርሜን፥
የስንት ዘመን ረሃቤን
ልጋረጠው በዓይንሽ አይኔን።
ልጅነቴን የዳኽኩበት፥ የስንት
ዘመን ፈለጌ
በናፍቆት ቋት ተሰግስጌ
በእግረ ሕሊና ጠርጌ
በትዝታ በዳሰሳ፥ በፈለግሽ የናዳ
ዳር
ስዋትት ስማስን በጣር
ዛሬ ያገኘሁሽ ባሣር
በስንት ዘመን የዕድሜ ምጥ
እውነት አንቺ እሷ ነሽ እርግጥ?!
መምሰል ትመስያለሽ
ማከልማ ታክያለሽ
የደም ግባቷን ተላብሰሽ
መጠሪያዋን ተሰይመሽ . . . .
ያቺን የኔን .... ያቺን የኔን
የኔን የመጀመሪያዬን
የጥንቴን የልጅነቴን
የስንት ዘመን ሕመሜን
የሕልም ዓለም ሰመመኔን
የት አረግሻት? የት ደበቅሻት?
ዋጥሻት? . . . .
አጥንቷን በአጥንትሽ ለብሰሽ
ወዟን በላቦትሽ ታጥነሽ
በልጅነቷ ልጅ ሆነሽ
ገጿን በግንባርሽ ነድፈሽ
አበቧን አደብዝዘሽ
መልኳን በመልክሽ አክስለሽ
ቡቃያዋን በዕድሜሽ ውጠሽ
በስም ብቻ እሷን ሆነሽ
ማነሽ? እውነት አንቺ ማነሽ
እኮ ንገሪኝ እሷ ነሽ?
እሑድ 27 ጃንዋሪ 2013
የቴዎድሮስ ስንብት ከመቅደላ - ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
የቴዎድሮስ ስንብት ከመቅደላ
ተስፋ ባጣ ምድረ በዳያንድ እውነት ይሆናል ዕዳ፡፡
እና ትንፋሼ አልሆነሽም፥ ሆኜብሽ መራር መካሪ
“ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ፣”
እውነት ላንቺ መች ተስፋ ናት፥ ጉስቁል ልሳንሽን ነክሳሽ
ክንድሽን ካዘለ ቅርስሽ፥ መጠላለፍ ሲሆን እጣሽ
ከእንግሊዝ የሞት አማልክት፥ መተናነቅ ሲሆን ድርሻሽ
መልመጥመጡ፥ መሽቆጥቆጡ፥ መስሎሽ ድንገት የሚያዋጣሽ
የኔ እውነት ሆነብሽ ዕዳሽ ፡፡ …..
ወራሪም ፈጣሪን ላያቅ
የጣለውን በስሏል እንጂ፥ ወድቋል ብሎ ግፉ ላያልቅ
መች ትተርፊያለሽ ኢትዮጵያ፥ ሕዋስሽ አብሮኝ ካልሠራ
አንገትሽ ብቻ መቅደላ፥ አፋፍ ወጥታ ብታበራ
የቀረው ሠራ-አከላትሽ፥ በየጥሻው ተዘርሮ
ከአባት በወረሽው ንፍገት፥ ነብዞ ደንዝዞ ተቀብሮ
ባጉል ወጌሻ ታጅሎ
እጅና እግርሽ ታሽቶ ዝሎ
እኔን ለጥንብ አንሳ ጥሎ፤
ከደቀቀ ከደከመ፥ ክንድሽ አልነሣ ካለ
ሞት እንጂ ለኔስ ምን አለ?.....
ሆኖም ጐስቋላ አልምሰልሽ፥ የሚያዝንልኝ አልፈልግም
ጠላትሽን በክንድሽ እንጂ፥ በእንባሽ ወዝ ባላሸንፍም
የልቤን ፍቅር በሰተቀር፥ እማወርስሽም ውል የለኝ
የኮሶ ሻጭ ልጅ ደሃ ነኝ፡፡ …..
እሑድ 13 ጃንዋሪ 2013
ቅዳሜ 12 ጃንዋሪ 2013
ወንድ ብቻውን ነው እሚያለቅስ- ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን

ከወዳጅ ከዘመድ ርቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ
ተሸሽጎ ተገልሎ፥ ተሸማቆ ተሸምቆ
ከቤተ-ሰው ተደብቆ
መሽቶ፥ የማታ ማታ ነው፥ ሌት ነው የወንድ ልጅ እንባው
ብቻውን ነው የሚፈታው፡፡ . . .
ብቻውን ነው የሚረታው፡፡ . . .
ችሎ፥ ውጦ፥ ተጨብጦ፥ ተማምጦ ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተወጥሮ
እንደደመና ተቋጥሮ
እውስጥ አንጀቱ ተቀብሮ . . .
መሽቶ፥ ረፍዶ፥ ጀምበር ጠልቆ
የጨለማ ድባብ ወድቆ
በእንቅልፍ ጥላ ሲከበብ፥ በዝምታ ሲዋጥ አገር
ፍጡር ሁሉ ተስለምልሞ፥ ብቸኝነት ብቻ ሲቀር . . .
Labels:
ቅኔ,
ፈርጦቹ,
poem,
poetry book,
Tsegaye G/Medhin
ሐሙስ 10 ጃንዋሪ 2013
እግር እንይ! (ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን)
poem in pdf እግር እንይ!(ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን)አርቀን ማስተዋል ማለት፣ የኛን ሥልጣኔ ድልድይእግር ማየት ነው ብለዋል፣ እስቲ እንግዲህ እግር እንይ!ያባቶችህ ያይን ድንበር፣ ከተረከዘ ሎሚ ሳያልፍአንተ ግን ጆቢራው-ዘራፍጠፍር አይወስንህ ጉብልጥሎ በዘመንህ ዕድልዓይንህ ባት አልፎ እንዲዋልል፤ቴህ ወዲያ ጀግንነት የለ፣ ተዚህ የከረረ ግዳጅባደባባይ የዱር ገደል፣ ስትናደፍ የእግር አዋጅሌሊቱን በየሌት- ‘ግለብ’፣ ቀኑን ጭምር በጠራራ
ረቡዕ 5 ዲሴምበር 2012
NILE: A Poem by Tsegaye Gebre-Medhin

I am the first
Earth Mother of all fertility
I am the Source
I am the Nile I am the African I am the beginning
O Arabia, how
could you so conveniently have forgotten
While your
breath still hangs upon the threads of my springs
O Egypt, you
prodigal daughter born from my first love
I am your Queen
of the endless fresh waters
Who rested my
head upon the arms of Narmer Ka Menes
When we joined
in one our Upper and Lower Lands to create you
bosom of my
being
How could you so
conveniently count down
In miserable
billions of petty cubic yards
The eternal
drops of my life giving Nile to you
Beginning long
before the earth fell from the eye ball of heaven,
O Nile, that
gush out from my breath of life
Upon the throats
of the billions of the Earth's thirsty multitudes,
O World, how
could you so conveniently have forgotten
That I, your first
fountain, I your ever Ethiopia
I your first
life still survive for you?
ሐሙስ 29 ኖቬምበር 2012
Tsegaye Gebre-Medhin Ethiopia's poet and playwright of the common people
- Yohannes Edemariam and Aida Edemariam
- The Guardian,
The poet and dramatist Tsegaye Gebre-Medhin, who has died aged 69, was considered Ethiopia's poet laureate. He was one of the most important literary figures that country has produced in the last hundred years, and certainly the best known, both within and outside it; his 1960s decision to write about the common man, rather than religion and royalty, marked the beginning of modern Ethiopian theatre. He wrote in English and was a translator of Shakespeare, but his real gift and achievement was to harness the considerable lyrical powers of his own, Ethiopian, languages.
Tsegaye was born in Boda, a village some 120km from the capital, to an Oromo father, who was away fighting the Italians, and an Amhara mother. (The two groups speak languages from entirely different linguistic groups, Cushitic and Semitic respectively; the latter has an alphabet of some 300 letters.) As many Ethiopian boys do, he also learned Ge'ez, the ancient language of the church, an Ethiopian equivalent to Latin; he also helped the family by caring for cattle. He was more unusual in beginning to write plays when at the local elementary school. At 16 he transferred to the Wingate school in Addis Ababa, where he developed an interest in pantomime; this was followed, in 1959, by a degree from the Blackstone School of Law in Chicago. He had not forgotten his first love, however; the following year he used a UNESCO scholarship to do an educational tour that included visits to the Royal Court Theatre in London and the Comédie Française, Paris.
The 1960s were an important decade. He returned to Ethiopia in 1960 to run the Municipality Company at the National Theatre and establish a school which produced a number of leading Ethiopian actors. Realising the usefulness of Shakespeare in the making of dangerous political points, he translated Macbeth and King Lear. He also translated Molière's Tartuffe, and wrote a play in English called Oda Oak Oracle, which was performed in theatres in Ethiopia, Britain, Denmark, Italy, Romania, Nigeria, Tanzania and the US, and still appears on reading lists in black studies departments. But it was Yekermew Sew (Tomorrow's Man) which established his place in Ethiopian theatre."Drawing from Ge'ez and Amharic and Orominya, he was able to coin phrases which, in normal Amharic language, don't exist, but are powerful and expressive," says Tamrat Gebeyehu, author of the Ethiopian entry in the World Encyclopedia of Contemporary Theatre. Thus it was "a pleasure to hear his characters talk, even though chances were you did not understand 50% of what they were saying." In 1966, aged 29, he became the youngest person ever to receive the Haile Selassie I Prize for Amharic Literature.
Briefly, he was appointed minister of culture, but Haile Selassie was deposed by Mengistu Hailemariam and, during the Red Terror in 1975, Tsegaye and the playwright Ayalneh Mulatu spent months together in a prison cell. Ayalneh, who remained friends with Tsegaye for the rest of his life, remembers a daily 11am roll call of men to be killed, and the day his own name came up. It was mispronounced, and Tsegaye seized on the mispronunciation to argue they had the wrong man, thus saving Ayalneh's life. They wrote poems and plays on the paper bags their food came in.
Agit-prop came into its own under the Marxist regime, as did Tsegaye's own brand of declamatory nationalism. He wrote Inat Alem Tenu (or Mother Cour- age, though he borrowed only the title) and Ha Hu be Sidist Wer (ABC in Six Months), which referred to the period of the emperor's deposition. In 1979 he helped to establish the theatre arts department at Addis Ababa University where he is remembered as being very strict and aloof. In the 1980s he also wrote historical plays about Ethiopian kings, one of which, Tewodros, was performed at the Arts Theatre in London in 1986. In 1993, after Mengistu Hailemariam was in turn deposed, he wrote a companion piece to Ha Hu be Sidist Wer. This was Ha Hu Weynis Pe Pu - A or Z, a play about peace, which the current regime banned.
There are persistent reports that the actors were beaten while on tour. Despite this, "I like to go out and communicate with the common folk of Ethiopia," Tsegaye wrote in 1999. "The peasant, the patriot, the soldier, the traitor, the housewife, the priest, the sheikh ... It is from them that I learn about my country and people. And generally their comments are accompanied by tears; their stories are mostly melancholy; their memories are bitter and tragic. It is that which I reflect in my writings. That is why my plays dwell on tragedy."
In 1998 he moved to New York to undergo dialysis, virtually unavailable in Ethiopia, and to be near his children. He remained active, promoting Ethiopian culture, until the end. In 2002 the African Union took one of his poems as its anthem. He is survived by his wife Lakech Bitew, three daughters, Yodit, Mahlet and Adey, and three sons, Ayenew, Estifanos and Hailu. Tsegaye Gebre-Medhin, poet and dramatist, born August 17 1936; died February 25 2006 http://www.guardian.co.uk/news/2006/may/03/guardianobituaries.booksobituaries
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)







