ልጥፎችን በመለያ poetry book በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ poetry book በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ዓርብ 27 ሜይ 2016
ማክሰኞ 8 ኤፕሪል 2014
“ወፍ እና ማለዳ” ነጠላ ግጥም ዳሰሳ - በአብደላ ዕዝራ
ወፍ እና ማለዳ
እንኳንስ
ችግኙ፥ ሰዎች የተከሉት
ሥር
ይዝ ነበረ፥ አዕዋፍ የዘሩት።
ዘንድሮ
ግን ወፎች፥ እንኳንስ ሊዘሩ
ናፍቆኛል
ማለዳ፥ መስማት ሲዘምሩ።
ወፎች ከማለዳ-
በምን ተቃቃሩ?!
ፅልመቱ ሲገፈፍ-
እንዳላበሰሩ፤
ማዜም ተስኗቸዉ-
ተዘግቶ ጀንበሩ
ወደሚነጋበት-
ወዴትስ በረሩ?!
-----------------------------------------------------
ምንጭ
= ሀ-ሞት [የግጥሞች ስብስብ]
ኄኖክ
ስጦታዉ
--------------------------------------------------------------
[ ገጣሚ
ኄኖክ ስጦታዉ የግጥም ስብስብ መፅሀፉን ሁለት ሶስቴ... ሊያሳትም ሲችል፥ በነፃ ሁላችንም እንድንመሰጥበት በድረ ገፁ ለቆታል። ገንዘብ እያስፈለገዉ ለሥነፅሁፍ ፍቅርና ልክፈት
ማደሩን አስቀደመ። ሀ-ሞት በጥሞና ለመነበብና ለማወያየት ጥበባዊ አቅም የቋጠረ መፅሃፍ ነዉ። ለጊዜዉ አንድ ዘለላ የተዋጣ ግጥሙን አብረን share በማድረግ በመጠኑ እናንብብ።
የምስጋና ያክል ነዉና - አብደላ ዕዝራ ]
---------------------------------------------------------------------------
<ወፍ እና
ማለዳ> አጭር እምቅ ተራኪ ግጥም ነዉ። ትረካዉ እንደ ማዉጋት የሚወረዛ ሳይሆን ገጣሚዉን ለመዘመዘ ጉዳይ መተንፈሻና ማዉጠንጠኛ ሆነ። የርዕሱ ስክነት ፈጠጠ እንጂ ጉጉት አልቀሰቀሰም። ርዕሱ ግጥሙ ዉስጥ ባደፈጠዉ ስንኝ በተተካ ያሰኛል፤ <ወፎች ከማለዳ በምን ተቃቃሩ?> የሚነሰንሰዉ አሻሚነት የሚከሶክስ፤ ከመነሻዉ በዉስጠምት -rhythm- የሚያባንን በሆነ። ተናጋሪዉ (persona) - የወንድም የሴትም አንደበት ሊሆን ይችላል - የቆረቆረዉ፥ ያሳሰበዉ የመምከን አባዜ አለ፤ እንዴት ሳይሆን ለምን በበለጠ ያብሰከስከዋል።
ደበበ
ሠይፉ <ወፊቱ> በሚለዉ ግጥሙ ቀን-ቀን አየሩን እየቀዘፈች አድማስ ሳይወስናት የቦረቀች ወፍ፥ ለአይን ያዝ ሲያደርግ መድናገሯን ተቀኘበት።
ኧረ
ምን መለሰሽ ?
ወደኋላ
ያዘሽ ?
መሸት
ከማለቱ ያደነቃቀፈሽ ?
ወፊቱ
በሌሊት ምን ይሆን ታስቢ
እኔኑ
መሰልሽኝ ጐጆሽ ስትገቢ።
ደበበ
የተናጋሪዉንና የወፊቱን የጓዳ ህይወት ቅዝቃዜ፥ የብቸኝነት ወጥመድ ... ህዋና የአራት ግድግዳ ስፋትና ጥበት የተወሳሰበበት ሥነልቦናዊና ኑሮዋዊ ጣጣ አነፃፀረ። ሄኖክ ግን ጐህ ሲቀድ ይህች ወፍ የማለዳ ብርቅነቷ ነዉ የረበሸዉ። መዝሙሯን፥ የአዲስ ቀን ምስራቿን እንዴት ነፈገችን ? ይቅርና እንደ ድምፅ ለእህልም -ወፍ ዘራሽ- ትበቃ የነበረዉ ከማለዳ ጋር ለምን ተቃቃሩ ? ቅኔያዊ፥ ዘይቤያዊ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን ሥር ከሰደደ ሥጋት ተፋትጐ የተቀጣጠለ ዕንቆቅልሽም ነዉ::
እንኳንስ
ችግኙ፥ ሰዎች የተከሉት
ሥር
ይዝ ነበረ፥ አዕዋፍ የዘሩት።
ዛሬ
ግን የአማርኛዉ ፈሊጥ “ወፍ ዘራሽ” ብሎም “ገና ወፍ ሳይንጫጫ” ምን አደበዘዘዉ ? ገጣሚዉ ቃላት ሳይከምር፥ እንደ ዘገባ ፊት ለፊት እሳቦቱን ሳይዘረግፍ ሰወኛ ዘይቤን በማጠላለፍ ዕምቅ ግጥም አስነብቦናል። በአርምሞ የአካባቢዉን ቁሳዊና ህሊናዊ ዐዉድ ከቃኘና ከታከከ በኋላ ጥያቄና ግርምታ ያደነደነዉን ስንኝ ያቀብለናል፤ ስናስብበት የተዳፈነዉ ረመጥ ፋታ አያዉቅም።
ማዜም
ተስኗቸዉ-
ተዘግቶ
ጀንበሩ
ወደሚነጋበት-
ወዴትስ
በረሩ?!
እኛ
ዘንድ መንጋት አቆመ ወይ ? ሰፈራችን ህይወታችን ለጨለማ ገብሮ፥ ለብርሃን ሽንቁር እስከመቼ አቴቴ ቢስ እንሆናለን ? ወፎች ጐህ ወደ ቋጠረዉ ተሰደዉ፥ ጀንበር እንደ ጣራ ተደፍኖ ሲቀር፥ ስጋቱ ያዉካል። “ጀምበር ካለ እሩጥ፥ አባት ካለ አጊጥ” እንደ ቅዠት ሊፈረካከስ ? ተስፋ ላለመቁረጥ የሄኖክ ግጥም ጀርባ እንዳለዉ ማወቅ ሊኖርብን ነዉ። የግጥሙን ተናጋሪ መጠራጠር እንጀምራለን፤ ቀን-ቀን እያንቀላፋ ለወፍ ዜማና ለንጋት መፍካት የሚቀሰቅሰዉስ ካጣ ? ይህንን ሄኖክ በሌላ ባለአንድ አንጓ ግጥሙ < ታሽጓል> የሚለዉን ግለሰብ ይገረምማል። እንዴት ከግሉ ደጃፍ ተገትሮ የራሱን በር ያንኳኳል ? የአደባባይ ሳይሆን ከዉስጡ የተጋረደዉ ንጋት ይብሳል።
ቢጠሩት
ላይሰማ፥
ልቤ
ተጠርቅሞ
የሚያንኳኳዉ
ማንነዉ፥
ደጃፉ
ላይ ቆሞ ?!
ይህ
ግለሰብ ብንን ሲል፥ በወፍና ንጋት ልክፈት ተቀንብቦ ፍለጋዉን አይገታም። እያደባ የደረሰባት ወፍ ግን < ጉጉት> ሆና ታሸማቅቃለች።
ከእርግቦች
መሐል፥
እርግብ
ተመስላ፤
“እርግብ
ናት”
ያልናቱ፥
ላባ
ተከልላ፤
ሥትከፍተዉ
አፏን፥
አየን
ጥርስ አብቅላ።
ያቺ
የምትዘምረዉ፥ ጨለማን ተርትሮ ብርሃን ሲያንሰራራ የሚያቅበዘብዛት ወፍ ሲያልም ይኑር፥ ወይስ ተስፋን እያማሰለ እያቦካ የህይወት በገናውን እየቃኘ የግሉን ዜማ ያፈልቅ የሆን ? የግጥሙ ጥንካሬ አለማብቃቱ። ይህን ንባብ በህዝብ ቅኔ - መንፈስ ለማርገብ ያክል - እንቋጨዉ። ፀሐይ የተባዕት መጠሪያ ሆኖ እንደ ሰምና ወርቅ ቢዳዳዉም፥ ለሄኖክ < ወፍ እና ማለዳ > ማንፀሪያም ነዉ። ማለዳ የናፈቀን ያህል፥ ፀሐይ የሚፈታተናትም ሄዋን ታቃስታለች።
በሐምሌ
በነሀሴ እንድያ ስዋትት
እንዴት
በመስከረም በፀሐይ ልሙት ?
****************************************
ምንጭ፡- ቤተ-መጻሕፍ ወጻሕፍት
እሑድ 16 ፌብሩዋሪ 2014
ማክሰኞ 12 ኖቬምበር 2013
*የሆድ አምላክ __~ኄኖክ ስጦታው
*የሆድ አምላክ __~ኄኖክ ስጦታው
ለማግኘቱ፣
ለማጣቱ
ለመውዛቱ፣
ለመንጣቱ
“እንጀራ”
ነው ለሀበሻ፣
“እህል
ውኃ” ምክንያቱ፡፡
ሕልውናው
የጸናበት፣
መወጣጫ
መሰላሉ
“የሆድ
አምላክ” ተቀብቷል፣
ይገለጣል “በእህሉ!”
ለረገጠው
መሬት ሳይሆን፣
ከእግሮቹ
በታች ላለው
ለማይነካው
ሲንጠራራ፣
ለሰማይ
ነው የቀረበው፡፡
“እህል
ውኃ” በሀበሻ፣
አምላካዊ
ክብር ለብሶ
“በጡር
አለው” ተሰቅዞ፣
“በክቡር ነው” ተወድሶ
ተሰጥቶ
ነው ለሰማያት፣
የሚዘራው
ምድር ታርሶ
“የሆድ
አምላክ” ካለበቱ፣
ከእኛው ሀገር ምግብ ነግሦ፡፡
* * *
የት
ነው ያለህ የሆድ አምላክ?!
ላነገሡህ
ምን አደረክ?!
ላመለኩህ
መች አጠገብክ?!
ምዕመንህ
ጠኔ ጥሎት፣ የሚበላው ተቸግሮ
በእርጥባን
መኖር በቅቶት፣ ሀገር ላገር ተዟዙሮ
“የሆድ
አምላክ” እውነት ካለህ፣
እስቲ
ይጥገብ ለዘንድሮ?!?
____________
2003 ዓ.ም
ኄኖክ
ስጦታው፣ ሀ-ሞት የግጥም መድበል
እሑድ 13 ጃንዋሪ 2013
ቅዳሜ 12 ጃንዋሪ 2013
ወንድ ብቻውን ነው እሚያለቅስ- ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን

ከወዳጅ ከዘመድ ርቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ
ተሸሽጎ ተገልሎ፥ ተሸማቆ ተሸምቆ
ከቤተ-ሰው ተደብቆ
መሽቶ፥ የማታ ማታ ነው፥ ሌት ነው የወንድ ልጅ እንባው
ብቻውን ነው የሚፈታው፡፡ . . .
ብቻውን ነው የሚረታው፡፡ . . .
ችሎ፥ ውጦ፥ ተጨብጦ፥ ተማምጦ ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተወጥሮ
እንደደመና ተቋጥሮ
እውስጥ አንጀቱ ተቀብሮ . . .
መሽቶ፥ ረፍዶ፥ ጀምበር ጠልቆ
የጨለማ ድባብ ወድቆ
በእንቅልፍ ጥላ ሲከበብ፥ በዝምታ ሲዋጥ አገር
ፍጡር ሁሉ ተስለምልሞ፥ ብቸኝነት ብቻ ሲቀር . . .
Labels:
ቅኔ,
ፈርጦቹ,
poem,
poetry book,
Tsegaye G/Medhin
ሐሙስ 10 ጃንዋሪ 2013
እግር እንይ! (ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን)
poem in pdf እግር እንይ!(ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን)አርቀን ማስተዋል ማለት፣ የኛን ሥልጣኔ ድልድይእግር ማየት ነው ብለዋል፣ እስቲ እንግዲህ እግር እንይ!ያባቶችህ ያይን ድንበር፣ ከተረከዘ ሎሚ ሳያልፍአንተ ግን ጆቢራው-ዘራፍጠፍር አይወስንህ ጉብልጥሎ በዘመንህ ዕድልዓይንህ ባት አልፎ እንዲዋልል፤ቴህ ወዲያ ጀግንነት የለ፣ ተዚህ የከረረ ግዳጅባደባባይ የዱር ገደል፣ ስትናደፍ የእግር አዋጅሌሊቱን በየሌት- ‘ግለብ’፣ ቀኑን ጭምር በጠራራ
ሰኞ 31 ዲሴምበር 2012
ከሞተች ቆይቷል
ሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ
ከሞተች ቆይቷል ብዙ ዘመን ሁኑዋል
ብዙ ነበር ጊዜው
ግን ፎቶግራፍዋ፣ ደብዳቤዋም አለ
በጠጉርዋ ጉንጉን የጠቀለለችው
ምን ቀነ ቀጠሮ ነው
ቀን የቀን ጎደሎ
የቀን ጥቁር መጥፎ፡፡
አበባ ሄድኩ ይዤ …
እዚያ አበባ አልጠፋም
በመቃብርዋ ውስጥ አበባ ተኝትዋል፡፡
ስሜቴ ፈነዳ ገላዬን በተነው
ነፍሴን ነቀነቃት
እንባዬ ወረደ ጉንጬን አረጠበው
ለተረሳ ነገር እንዴት ያለቅሳል ሰው!
ለተረሳ ነገር
ምን ጊዜው ቢረዝም . . .
የዚህ አለም ጣጣ እንከራተተኝ
የዚህ አለም ስቃይ እየቦረቦረኝ -
ሲጨንቀኝ ሰውነት
ፍቅሬ ይሁን ያንቺ የኔ መቃብር ቤት፤
ህይወት ነዶ ጠፍቶ ሞት ፍሙን ሲያዳፍን
ያን ጨለማ ጉዋዳ ሄጄ ልተኛበት፡፡
ይመስላል ዘላለም . . .
ረቡዕ 5 ዲሴምበር 2012
NILE: A Poem by Tsegaye Gebre-Medhin

I am the first
Earth Mother of all fertility
I am the Source
I am the Nile I am the African I am the beginning
O Arabia, how
could you so conveniently have forgotten
While your
breath still hangs upon the threads of my springs
O Egypt, you
prodigal daughter born from my first love
I am your Queen
of the endless fresh waters
Who rested my
head upon the arms of Narmer Ka Menes
When we joined
in one our Upper and Lower Lands to create you
bosom of my
being
How could you so
conveniently count down
In miserable
billions of petty cubic yards
The eternal
drops of my life giving Nile to you
Beginning long
before the earth fell from the eye ball of heaven,
O Nile, that
gush out from my breath of life
Upon the throats
of the billions of the Earth's thirsty multitudes,
O World, how
could you so conveniently have forgotten
That I, your first
fountain, I your ever Ethiopia
I your first
life still survive for you?
እሑድ 28 ኦክቶበር 2012
"የኢትዮጵያ ግጥም ፈርጥ" ለአጼ ይስሓቅ በዘመኑ ከተገጠመላቸው የተወሰደ
ዓፄ ይስሐቅ
ቀዳማዊ አጼ ይሥሓቅ
በዙፋን ስማቸው "ዳግማዊ ገብረ መስቀል" ሲባሉ እ.ኤ.አ ከ1414-1429 የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የነበሩ ናቸው።
የቀዳማዊ አጼ ዳዊት ሁለተኛ ወንድ ልጅ ሲሆኑ የቀዳማዊ ቴዎድሮስ ታናሽ ወንድም ናቸው።
በግብጽ ቆብጦች ላይ በሚካሄድው ዘመቻ ምክናያት ብዙ ኮብቶች ወደኢትዮጵያ በዚሁ ዘመን ተሰደዱ። ከነዚህ ውስጥ ፋቅር አል-ዳዋ የተሰኘው የግብጹ ማምሉክ ባለሟል ይገኝበታል። ይህ ባለሟል በይስሓቅ ግዛት ውስጥ ተሰሚነት በማግኘቱ የአገሪቱን የግብር ስርዓት በመለወጥ በግብጽ ማምሉኮች በሚሰራበት መልኩ እንዲሆን አድርጓል። የንጉሱንም አለባበስ በመቀየርና መስቀል እንዲይዝ በማድረግ ንጉሱ ከቀሪው ህዝብ ለየተ እንዲል አድርጓል። በኋላም በራሳቸው በግብጽ እስላሞች መካከል በተነሳ ጠብ የቁስክፍለ ሃገር ገዢ የነበርው አሚር አል-ቱንቡጋ አል-ሙፍሪቅ በአጼ ይስሓቅ መንግስት ባለሟልነትን አግኝቶ በኋላ የንጉሱ ሰራዊት እንዲሻሻል አድርጓል። ይህ ግብጻዊ ለኢትዮጵያው ሰራዊት ካስተዋወቃቸው ነገሮች ውስጥ የእሳት ችቦ መወርወሪያ ዘዴንና የሻሞላ ውጊያን ይይዛሉ። እንደ ታሪክ አጥኝው ጅ.ቢ.ኸንቲንግፎርድ አባባል ከሆነ የኢትዮጵይ ነገስታት ቋሚ ዋና ከተማ ማድረግ ያቆሙት በዚሁ ንጉስ ዘመን ነበር።
በግብጽ ቆብጦች ላይ በሚካሄድው ዘመቻ ምክናያት ብዙ ኮብቶች ወደኢትዮጵያ በዚሁ ዘመን ተሰደዱ። ከነዚህ ውስጥ ፋቅር አል-ዳዋ የተሰኘው የግብጹ ማምሉክ ባለሟል ይገኝበታል። ይህ ባለሟል በይስሓቅ ግዛት ውስጥ ተሰሚነት በማግኘቱ የአገሪቱን የግብር ስርዓት በመለወጥ በግብጽ ማምሉኮች በሚሰራበት መልኩ እንዲሆን አድርጓል። የንጉሱንም አለባበስ በመቀየርና መስቀል እንዲይዝ በማድረግ ንጉሱ ከቀሪው ህዝብ ለየተ እንዲል አድርጓል። በኋላም በራሳቸው በግብጽ እስላሞች መካከል በተነሳ ጠብ የቁስክፍለ ሃገር ገዢ የነበርው አሚር አል-ቱንቡጋ አል-ሙፍሪቅ በአጼ ይስሓቅ መንግስት ባለሟልነትን አግኝቶ በኋላ የንጉሱ ሰራዊት እንዲሻሻል አድርጓል። ይህ ግብጻዊ ለኢትዮጵያው ሰራዊት ካስተዋወቃቸው ነገሮች ውስጥ የእሳት ችቦ መወርወሪያ ዘዴንና የሻሞላ ውጊያን ይይዛሉ። እንደ ታሪክ አጥኝው ጅ.ቢ.ኸንቲንግፎርድ አባባል ከሆነ የኢትዮጵይ ነገስታት ቋሚ ዋና ከተማ ማድረግ ያቆሙት በዚሁ ንጉስ ዘመን ነበር።
ረቡዕ 17 ኦክቶበር 2012
የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞች
| በሙሉ ግጥሙን ለመመልከት [PDF] |
ከአጼ ቴዎድሮስ፣ አጼ ዮሐንስ፥ አጼ ምኒልክ፥ እቴጌ ጣይቱ፥ ልጅ ኢያሱ፥ ንግሥት ዘውዲቱ፥ ተፈሪ፣ አጼ ኃይለ ሥላሴ፣ ደርግ፣ ወዘተ ጋር የተያያዙ ብዙ በርካታ ጉዳዮችም በስፋት በግጥሞቻቸዉ ዉስጥ ተነሰተዋል። ሼህ ሁሴን ጅብሪል አፄ ሚኒሊክ አድዋ ላይ ከጣሊያን ጋር እንደሚዋጉና በጦርነቱም ድል እንደሚቀናቸዉ ቀድመዉ ተንብየዋል፡ ከአድዋ ጦርነትም በሁዋላ ጣሊያን ተመልሶ ኢትዮጵያን እንደሚወርና ከአምስታመት ቆይታ በሁዋላ ተመልሶ ከሀገር እንደሚባረር፣ ሆኖም በነዚህ የአምስት አመታት የቆይታ ጊዜ ዉስጥ ብዙ ሰዉ በግፍ እንደሚገደል ጭምር ተንብዬዉ እንደነበር ይነገራል። ለምሳሌ ያክልም፣ የጽሑፍ ጥናት ገና ያልተጠናቀቀ ቢሆንም፣ የሼህ ሁሴንን ትንቢታዊ ግጥሞች ለማጥናትና ለማነጻጸር፣ ለሚፈልጉ ምሁራንና ተማሪዎች ይረዳል ብለዉ በማሰብ ዶ /ር ጌቴ ገላዬ 1996 ዓ.ም በእጅ ተጽፎ ፎቶ ኮፒ ከተደረገ አንድ አነስተኛ ደብተር አግኝተዉ ካጠናቀሩትና በኢንተርኔት እንዲሰራጭ ካደረጉት ብዛት ያላቸዉን የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢታዊ ግጥሞችን ካተተ መጣጥፋቸዉ ዉስጥ ከዚህ የሚከተሉት ሁለት ግጥሞች መዉሰድ ይቻላል።
ሥራቸው ባለጌ አህያ የሚበሉ
ባሕር ወዲያ ማዶ ክፉ ሰዎች አሉ፣
ሐበሻን ለመውረር ሐሳብ ያስባሉ
የኋላ የኋላ መምጣት ይመጣሉ
አምስት ዓመት ገዝተው ወዲያው ይሄዳሉ።
ድንጋይ ዱቄት አርገው መንገድ የሚያበጁ
ገመድን ዘርግተው መብራት የሚያበጁ
አህያ የሚያርዱ አሞራ የሚፈጁ
መጡ እየተማሩ ሐበሻን ሊያበጁ
ማማሩን አማረች ግን ብዙ ሰው ፈጁ።
ስለ ወታደራዊ አገዛዝ የደርግ መንግስትና በጊዜዉ ስለ ነበረዉ የመሬትና ሹመት ጣጣ አስመልከተዉ ሼህ ሁሴን ጅብሪል በትንቢታዊ ግጥማቸዉ እንዲህ ብለዉ አስጠንቅቀዉ እንደነበርም ይነገራል።
በሰማይ ቀበሌ መላኢሞች ሲያወጉ
በአጼ መባል ቀርቶ ይባላል በደርጉ
ያን ጊዜ በዱአ እንዳትዘነጉ
መሬትና ሹመት እንዳትፈልጉ።
ዓርብ 21 ሴፕቴምበር 2012
Dr Kebede Michael's poetry book ታሪክና ምሳሌ ፪ /tarik ena mesale/ part 2 in [PDF]
Dr Kebede Michael was one of the giants in the field f education and literature in Ethiopia. He wrote a total of 26 books including a wide range of translations from various languages. From 1940 to1970, he wrote Amharic school textbooks in which he provided generations of Ethiopian students with enlightening ideas about a wide range of issues and disciplines.
His writings were in both prose and poetry and his poems follow rhyming and writing styles of his own. He also translated - among many - Romeo and Juliet, as well as Macbeth of William Shakespeare. Kebede Michael’s literary works reflect many shades of character and behavior of the Ethiopian society. The contents of many of his books are on history, education, development, philosophy, religion, science and so on.
He worked as an inspector in the Ministry of Education, as Deputy Director in the Ministry of Foreign Affairs (1942), as Director of the National Library (1944), as Director General of the Ministry of Education, and as a Cabinet Minster in the Imperial Palace. He was also delegated to many international conferences including at the United Nations in New York.
He received the first Prize for Literature from Emperor Haileselassie. He also received awards from governments of France, Germany, Italy, USSR and Mexico. And in 1990, he received an Honorary Doctorate Degree from Addis Ababa University for his unparalleled excellence in literature as well as for inspiring generations of Ethiopian authors and writers.
Dr. Kebede Michael died on 12 November 1998 at the age of 82. No other Ethiopian in the country’s history so far has been able to write as extensively on a wide variety of disciplines as did Kebede Michael.
His contributions are enormous to the development of education and literature. And he may be deceased, yet his legacy will live on forever; and Ethiopians are greatly thankful to him.
ታሪክና ምሳሌ ፪ በከበደ ሚካኤል ከተደረሱት ሁለት ክፍል ታሪክና ምሳሌ መጽሃፎች ሁለተኛው ክፍል ነው። መጽሃፉ ስለ ሃገርና ቀን ተቀን አኗኗር ዘይቤወች ምክሮችን በምሳሌ የሚያቀርብ ነው።
TARIK ENA MESALE 2
|
Dr Kebede Michael's poetry book ታሪክና ምሳሌ ፩ /tarik ena mesale/ part one in [PDF]
Dr Kebede Michael was one of the giants in the field f education and literature in Ethiopia. He wrote a total of 26 books including a wide range of translations from various languages. From 1940 to1970, he wrote Amharic school textbooks in which he provided generations of Ethiopian students with enlightening ideas about a wide range of issues and disciplines.
His writings were in both prose and poetry and his poems follow rhyming and writing styles of his own. He also translated - among many - Romeo and Juliet, as well as Macbeth of William Shakespeare. Kebede Michael’s literary works reflect many shades of character and behavior of the Ethiopian society. The contents of many of his books are on history, education, development, philosophy, religion, science and so on.
He worked as an inspector in the Ministry of Education, as Deputy Director in the Ministry of Foreign Affairs (1942), as Director of the National Library (1944), as Director General of the Ministry of Education, and as a Cabinet Minster in the Imperial Palace. He was also delegated to many international conferences including at the United Nations in New York.
He received the first Prize for Literature from Emperor Haileselassie. He also received awards from governments of France, Germany, Italy, USSR and Mexico. And in 1990, he received an Honorary Doctorate Degree from Addis Ababa University for his unparalleled excellence in literature as well as for inspiring generations of Ethiopian authors and writers.
Dr. Kebede Michael died on 12 November 1998 at the age of 82. No other Ethiopian in the country’s history so far has been able to write as extensively on a wide variety of disciplines as did Kebede Michael.
His contributions are enormous to the development of education and literature. And he may be deceased, yet his legacy will live on forever; and Ethiopians are greatly thankful to him.
|
ሐሙስ 16 ኦገስት 2012
The Earth ~Gods KahlilGibran {short stories}
Kahlil GibranThe
When the night of the twelfth aeon fell,
And silence, the high tide of night, swallowed the hills,
The three earth−born gods, the Master Titans of life,
Appeared upon the mountains.
Rivers ran about their feet;
The mist floated across their breasts,
And their heads rose in majesty above the world.
Then they spoke, and like distant thunder
Their voices rolled over the plains.
FIRST GOD
The wind blows eastward;
I would turn my face to the south,
For the wind crowds my nostrils with the odours of dead things.
SECOND GOD
It is the scent of burnt flesh, sweet and bountiful.
I would breathe it.
FIRST GOD
It is the odour of mortality parching upon its own faint flame.
Heavily does it hang upon the air,
And like foul breath of the pit
It offends my senses.
ሰኞ 13 ኦገስት 2012
Dr Kebede Michael's book የትንቢት ቀጠሮ.pdf
የትንቢት ቀጠሮ
የትንቢት ቀጠሮ
በደራሲ ከበደ ሚካኤልየተደረሰ የቴያትር መጽሐፍ ነው።
ለሁለተኛ ጊዜ በ ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ታተመ።
file size: 7.78 MB, MIME type: application/pdf, 54 pages)
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)




