ይህ ጽሑፍ በመጠኑም ቢሆን ስለገብረ ክርስቶስ ደስታ ማንነት የሚያትት ሆኖ ስላገኘሁት የዶክተር ፍቃደ አዘዘን ንግግር በፎቶ መልክ ገጼ ላይ ለጥፌዋለሁ፡፡ርግጥ ውይይቱ የተካሄደው የዛሬ አስር ዓመት ገደማ ቢሆንም ቅሉ ፣ ካለው ኪነጥበባዊ ፋይዳ አንጻር ለአጥኚዎች እንደ አንድ ግብዓት ማገልገሉ እሙን ነው፡፡ ውድ የእልፍኜ ታዳሚያን ፣ በገጣሚና ሰዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ ሥራዎች እና የሕይወት ጉዞ ላይ ተጨማሪ መረጃ ካላችሁ በኢሜል አድራሻዬ ትልኩልኝ ዘንድ መልካም ፍቃዳችሁን እለምናለሁ፡፡
ልጥፎችን በመለያ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ረቡዕ 16 ኦክቶበር 2013
ሐሙስ 17 ጃንዋሪ 2013
እኔ እወድሻለሁ /ገብረክርስቶስ ደስታ /
ሰኞ 31 ዲሴምበር 2012
ከሞተች ቆይቷል
ሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ
ከሞተች ቆይቷል ብዙ ዘመን ሁኑዋል
ብዙ ነበር ጊዜው
ግን ፎቶግራፍዋ፣ ደብዳቤዋም አለ
በጠጉርዋ ጉንጉን የጠቀለለችው
ምን ቀነ ቀጠሮ ነው
ቀን የቀን ጎደሎ
የቀን ጥቁር መጥፎ፡፡
አበባ ሄድኩ ይዤ …
እዚያ አበባ አልጠፋም
በመቃብርዋ ውስጥ አበባ ተኝትዋል፡፡
ስሜቴ ፈነዳ ገላዬን በተነው
ነፍሴን ነቀነቃት
እንባዬ ወረደ ጉንጬን አረጠበው
ለተረሳ ነገር እንዴት ያለቅሳል ሰው!
ለተረሳ ነገር
ምን ጊዜው ቢረዝም . . .
የዚህ አለም ጣጣ እንከራተተኝ
የዚህ አለም ስቃይ እየቦረቦረኝ -
ሲጨንቀኝ ሰውነት
ፍቅሬ ይሁን ያንቺ የኔ መቃብር ቤት፤
ህይወት ነዶ ጠፍቶ ሞት ፍሙን ሲያዳፍን
ያን ጨለማ ጉዋዳ ሄጄ ልተኛበት፡፡
ይመስላል ዘላለም . . .
ቅዳሜ 8 ዲሴምበር 2012
ረቡዕ 5 ዲሴምበር 2012
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)