ልጥፎችን በመለያ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ

ረቡዕ 16 ኦክቶበር 2013

ትዝታ ዘ-ገብረ ክርስቶስ ደስታ ፡ ገጣሚ - ሰዓሊ? ወይስ ሰዓሊ - ገጣሚ? - በዶክተር ፍቃደ አዘዘ


ይህ ጽሑፍ በመጠኑም ቢሆን ስለገብረ ክርስቶስ ደስታ ማንነት የሚያትት ሆኖ ስላገኘሁት የዶክተር ፍቃደ አዘዘን ንግግር በፎቶ መልክ ገጼ ላይ ለጥፌዋለሁ፡፡ርግጥ ውይይቱ የተካሄደው የዛሬ አስር ዓመት ገደማ ቢሆንም ቅሉ ፣ ካለው ኪነጥበባዊ ፋይዳ አንጻር ለአጥኚዎች እንደ አንድ ግብዓት ማገልገሉ እሙን ነው፡፡ ውድ የእልፍኜ ታዳሚያን ፣ በገጣሚና ሰዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ ሥራዎች እና የሕይወት ጉዞ ላይ ተጨማሪ መረጃ ካላችሁ በኢሜል አድራሻዬ ትልኩልኝ ዘንድ መልካም ፍቃዳችሁን እለምናለሁ፡፡

[PDF]

 






ሐሙስ 17 ጃንዋሪ 2013

እኔ እወድሻለሁ /ገብረክርስቶስ ደስታ /



















ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚሊዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንችን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ።
እኔ እወድሻለሁ
የሰማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ፅጌ-ረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደ ሎሚ ሽታ፡፡
እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
እኔ እወድሻለሁ፣
አበባ እንዳየ ንብ፡፡

ሰኞ 31 ዲሴምበር 2012

ከሞተች ቆይቷል


ሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ

ከሞተች ቆይቷል ብዙ ዘመን ሁኑዋል
ብዙ ነበር ጊዜው
ግን ፎቶግራፍዋ፣ ደብዳቤዋም አለ
በጠጉርዋ ጉንጉን የጠቀለለችው
ምን ቀነ ቀጠሮ ነው
ቀን የቀን ጎደሎ
የቀን ጥቁር መጥፎ፡፡
አበባ ሄድኩ ይዤ …
እዚያ አበባ አልጠፋም
በመቃብርዋ ውስጥ አበባ ተኝትዋል፡፡
ስሜቴ ፈነዳ ገላዬን በተነው
ነፍሴን ነቀነቃት
እንባዬ ወረደ ጉንጬን አረጠበው
ለተረሳ ነገር እንዴት ያለቅሳል ሰው!
ለተረሳ ነገር
ምን ጊዜው ቢረዝም . . .
የዚህ አለም ጣጣ እንከራተተኝ
የዚህ አለም ስቃይ እየቦረቦረኝ -
ሲጨንቀኝ ሰውነት
ፍቅሬ ይሁን ያንቺ የኔ መቃብር ቤት፤
ህይወት ነዶ ጠፍቶ ሞት ፍሙን ሲያዳፍን
ያን ጨለማ ጉዋዳ ሄጄ ልተኛበት፡፡
ይመስላል ዘላለም . . .

ቅዳሜ 8 ዲሴምበር 2012

ሃ ገ ሬ በ ገብረክርስቶስ ደስታ



ሃ ገ ሬ
{ሰአሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ}

አገሬ ውበት ነው፣

ለምለምና ነፋስ የሚጫወትበት፣

ፀሃይ የሞላበት፣ ቀለም የሞላበት።

አገሬ ቆላ ነው፣ ደጋ ወይና ደጋ፣

እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ እስኪነጋ።

አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ፣

አገሬ ጅረት ነው ገደልና ሜዳ፣

ውበት ነው በበጋ ፀሃይ አትፋጅም፣

ክረምቱም አይበርድም፣

አይበርድም፣ አይበርድም። 

አገሬ ጫካ ነው፣

እንሰሳት አራዊት የሚፈነጩበት፣

በወጥመድ ሳይገቡ ሳይነካቸው ጠላት።

እዚያ አለ ነፃነት፣

ረቡዕ 5 ዲሴምበር 2012

በሰዓሊና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ/ እኔ እወድሻለሁ


ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚሊዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንችን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ።
እኔ እወድሻለሁ
የሰማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ፅጌ-ረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደ ሎሚ ሽታ፡፡
እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
እኔ እወድሻለሁ፣
አበባ እንዳየ ንብ፡፡