2013 ጁን 29, ቅዳሜ

ከሰባራ ባቡር እስከ ዮሐንስ ሰፈር (የቮልስ መኪና ትዝታዬን የቀሰቀሰው የዘንድሮው የመንግስት ባጀት መዝጊያ)

በ-ኄኖክ ስጦታው

/ቮልስ ዋገን ገዝተህ “ፒምፕ” ለማድረግ ቁም ስቅልህን የምታየው ወዳጄ፣ ይሄ ነገር አንተንም ይመለከታል እና አድምጠኝማ፡፡/ አውነቴን ነው፤ ቮልስ ለማደስ የሚወጣ ገንዘብ መኪናው ዋጋ ላይ ከአንድ መቶ ብር በላይ እንደማይጨምር ከራሴ ተሞክሮ ብትማር ነው የሚያዋጣህ/

ሁሌም የማስታውሰው ተረብ አለ፡፡ ቮልስ መኪና እንደገዛሁ “ልወዝወዘው በእግሬ” የሆነ ወዳጄ ክፉኛ ሞራሌን ያደቀቀበት ተረብ፡፡ መቼስ ላይችል አይሰጥም ነውና ቻልኩት፡፡ እንደማያልፍ የለ አለፈ፡፡ መኪናዋን የገዛኋት ሰሞን መልኳ ጠይም ነበር፡፡ ጠይምነቷ የቅብ ሳሆን የዝገት መሆኑን ልብ በሉ፡፡ ይህ ወዳጄ መኪናዋን እንዳያት ሆዱን ይዞ ስቆ ሲያበቃ፡-

“እንዴ !!! ይህችን መኪናን ያመረተው ፋብሪካ እኮ አሁን ዲዲቲ ማምረቻ እንደሆነ ታውቃለህ??! ” አለኝና ድጋሚ ሳቀ፡፡ ጥርሱን ባረግፈው ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ጥርሱን እንዲያረግፈው ረግሜው ማለፍ መምረጤ ግን ጠቅሞኛል፡፡ ቮልሷን መኪና ለማድረግ(ይቅርታ፣ መኪና ለማስመሰል) ያወጣሁት ወጪ ላይ የጥርስ ዋጋ ቢታከልት “እርም መኪና” የሚያስብል ነበረ፡፡

“የአገልግሎት ዘመኗን ድሮ ገና ከጨረሰች ቮልስ ጋር ለምን ትዳረቃለህ??” ያለኝ ባለሃብትም ነበር፡፡
/መኪና እና ስቴኪኒ በማይጣልበት አገር ውስጥ ነን፡፡ ለማን ብለን ነው የምንጥለው/

የሰባራ ባቡር አካባቢን የማውቀው በዚህች መኪና ዘመን ነው፡፡ ዲኮር አድራጊዎቹም የሆነ የሆነ ቦታ ሲያገኙኝ “እንዴት ናት ቮልስህ??” ብለው ከሚጠይቁኝ ጥያቄ ተነስቼ መቼም ቢሆን እንደማይረሱኝ ድምዳሜ ላይ ደርሻለሁ፡፡ ካለማጋነን፣ አዲስ መኪና ለማስዋብ ከሚለጠፍ ስቲከር ተቆርጦ የሚጣለውን አንስቼ የኔዋ መኪና ላይ በመለጠፍ ለማስዋብ ያደረኩት ጥረት ከመኪናዬ በላይ እኔን እዲያስታውሱ ያስገድዳቸዋልና፡፡

ሰሞኑን የባጀት መዝጊያ ወቅት ነው፡፡ እግር ጥሎኝ በሰባራ ባቡር አካባቢ ሳልፍ ቮልሴ ትዝ አለችኝ፡፡ እንዳስታውሳት ምክንያቱ ደግሞ የመንግስት ተሸከርካሪዎች ዲኮር በማስደረግ ተጠምደው አይቼ ነው፡፡ አብዛኛዎቹ መኪኖች አዲስ ናቸው፡፡ ምን እያደረጉ ነው??

ስቲከር ያስለጥፋሉ!

መጋጫ ያስገጥማሉ!

በመብራት እና ፈረፋንጎ ላይ የሚገጠሙ “ክሮሞችን” ያስለጥፋሉ!

የወንበር ልብስ ያለብሳሉ . . . .

ይህ ሁሉ መኳኳል ለምን አስፈለገ?? ለነዚህ መኪናዎቹ በውበት ላይ ውበት መጨመር ለዕድገታችን “መሳለጥ” ፋዳው ምንድነው??? ሚጢጢዬ ስቲከር ለማስለጠፍ የሚወጣ ገንዘብ /“ፈርቅ”ን ጨምሮ/ ዘርፈ ብዙ ሽንቁር ላላት አገራችን ስንት ቀዳዳ ይደፍናል?? /ያውም በያንዳንዱ ግዢ ላይ አየር የሚይዙ ፐርቸዘሮች በበዙባትአገር/

መኪናዎቹ'ኮ አዲስ ናቸው፡፡ ምንም ባይደረግባቸውም ያምራሉ፡፡ መሽቀርቀራቸውን ለምን ፈለጉ??? ወይስ ባጀቱ ቢመለስ ተመልሶ የማይመጣ መስሏቸው??

ውድ የጦማሬ አንባቢያንን እና ቋሚ ተከታታዮች

ውድ የጦማሬ አንባቢያንን እና ቋሚ ተከታታዮች፤  አዲሱ የፌስ ቡክ ገፄን ታውቁት ዘንድ ጋበዝኳችሁ፡፡ like በማድረግ በቋሚነት ይከታተሉ፡፡


          ሄኖክ ስጦታው 

ግማሽ ህልም


*
*

እኔና ጓደኛዬ አብረን ያለንበትን መኪና በተደጋጋሚ ትራፊክ ፖሊስ ያስቆምና ይቀጣዋል፡፡ ጎን ለጎን በፈረስ እየጋለብንም ከሆነ ከየት መጣ ሳይባል ትራፊክ ይይዘንናሕገወጥ ግልቢያ አድርጋችኋል! መንጃ ፍቃድ!!”ይለናል፡፡

ጓደኛዬ ከኔ የበለጠ በመማረሩ የትራፊክ ሞተርሳይክል ከአሮጌ ተራ በርካሽ ገዝቶ አሸክሞ መጣ፡፡ /ይኼኛው ሞተር ሳይክልየኢትዮ- ቻይና ወዳጅነት መንገድከመሰራቱ በፊት በእርዳታ ያገኘነው አይነት ስለሆነ ለመንዳት ብዙም አልተቸገርኩም፡፡ /

በመጀመሪያ እሱን ከኋላዬ አስቀመጥኩና አቀማመጡን እንደቻለበት እና እንዳልቻለበት በሚገባ አጤንኩ፡፡ ለከረፉ አይሰጥም፡፡ መቼስ ፖፖ ላይ የተቀመጠ ብላቴና ቢያስመስለውም፡፡

ጉዞ ወደአቢዮትአደባባይ ! ሞተሯ በጣም ፈጣን ናት፡፡ ከመቼው እንደደረስን አላስታውሰውም፡፡ አብዮት አደባባይ ላይ ቀይ መብራት ይዞን እንደቆምን አንድ ጥቁር እና ግዙፍ ትራፊክ ከሩቁ በክፉ አይን እየተመለከተን እንደሆነ አስተዋልኩ፡፡

የሞተሯን አቅጣጫ ወደ ኢሚግሬሽን አዞርኩና የመብራቱን መልቀቅ ተከትዬ ተንቀሳቀስኩ፡፡ የሞተሩ ጉልበት ከመንተፋተፉ ባሻገር ካንዴላውን ዘይት ሳያገኘው እንደማይቀር ጠረጠርኩ፡፡

አሁን ስለካንዴላ የማሰቢያ ጊዜ ላይ አይደለንም፡፡ አንደምንም ብለህ ከኋላ ካለው ትራፊክ ወታደር እራሳችንን እናድን፡፡አለኝ ጓደኛዬ፡፡ አልሰማሁትም፡፡ ብሰማውም ለውጥ አልነበረውም፡፡ እንደዛ በብርሃን ፍጥነት ከአዲሱቅድመ ዓያትመንደር እዚህ ያደረሰን ሞተር እየተንተፋተፈ እኛ ወደፈለግንበት ሳይሆን ወዳልፈለግንበት ማምራት ጀመረ፡፡ የነዳጅ መስጫውን ብረግጠው ከባድ ማርሽ ባስገባ ምንም ለውጥ አላመጣም፡፡

እናም እንደፈራነው ሆነ፡፡ ትራፊክ ፖሊሱ ጋር ስንደርስ ፍሬኑን ሳልይዘው ሞተሩ በራሱ ጊዜ ቆመ፡-

በቃ! ተበላን!!” አለኝ ጓደኛዬ ወደጆሮዬ ውስጥ ገብቶ፡፡ እንዳለውም አልቀረ፡፡ ትራፊኩ፡-

መንጃ ፍቃድ!!” አለ ወታደራዊ ሰላምታውን አቅርቦ ሲያበቃ፡፡

ምን አጠፋሁ ጌታዬ? ” አልኩት እየተርበተበትኩ፡፡

ሃሳብ በመቀየር አቅጣጫ በመቀየር . . . ደንብ ተላልፈሃል፡፡

ዋሌቴን አውጥቼ መንጃ ፍቃዴን ስበረብር አጣሁት፡፡ የዕቁብ ደብተር ብቻ ነው እንዴ የያዝኩት?? ይሄን እቁብ ደግሞ መቼ ነው የጀመርኩት??

ብቻ፣ ውስጡ ሃምሳ ብር አስገብቼ ለትራፊኩ አቀበልኩት፡፡ ምንም አላለም፡፡ የብሩን ፎርጂድ አለመሆን አጥንቶ ሲያበቃ ደብተሩን ብቻ መለሰልኝ፡፡

ይኼ ሞተር በተደጋጋሚ ጥፋቶች ይታወቃል፤ ታርገው ለሌሎች ትራፊኮች የተበተነ ሲሆን ካስቆሟችሁ ይህን ጽሑፍ አሳዩዋቸው፡፡ብሎ በብጣሽ ወረቀት ላይ የሆነ ነገር ጽፎ ሰጠኝ፡፡ አንድ ቃል ብቻ ነው የተነበበልኝ፡-

የተቀጣ!”


2013 ጁን 28, ዓርብ

“ፍሩት” ቅድመ-ክትባት---- ኄኖክ ስጦታው




ወዳጄ ነው፡፡ የፍራፍሬ ጭማቂ መሸጫ ሱቅ አለው፡፡ የኑሮ ዘይቤው እና አመለካከቱ በሁለት ነገር የተገደበ ነው፡፡ በፍራፍሬ ጥቅም እና በፍራፍሬ ጥቅም ብቻ፡፡ ጭማቂ ልጠጣ በሄድኩባቸው ጊዜያት ሁሉ የገንዘብ መቀበያው ሳጥን ውስጥ  አላጣውም፡፡ የበሰለ ብርቱካን የመሰለ ፊቱን በፈገግታ አጅቦ ሰላም ይለኛል፡፡ ጭማቂው እስከሚመጣ አንዳንድ ፍልስፍናዎቹን ያዥጎደጉድልኛል፡፡

“የኛ ሰው ሲታመም ብቻ ነው አትክልትና ፍራፍሬ ይዘንለት የምንሄደው፡፡ በጤነኛነቱ ሰዓት ግን አረቄ ካልጋበዝንህ ብለን እናስጨንቀዋለን፡፡” ይለኛል፡፡

“እና ምን ማድረግ ነበረብን???” ብዬ እጠይቀዋለሁ ምን እንደሚለኝ ለመስማት፡፡

“ፍራፍሬ ሳትታመም በፊት ከተመገብክ እንደ ክትባት ነው፡፡ ከታመምክ በኋላ ግን ለጠያቂዎች የምታቀርበው የቡና ቁርስ ይሆናል፡፡” ይለኛል፡፡


ከሰባት ዓመታት በፊት ፣ ካልተሳካው አብዮት ጋር ተያይዞ የስራ ማቆም አድማና የንግድ ቤቶች መዘጋትን ተከትሎ ሥራው ላይ ከባድ ፈተና ገጥሞት እንደነበር የነገረኝን አልረሳውም፡፡ ለጭማቂ እና ለችርቻሮ ያዘጋጃቸው አትክልትና ፍራፍሬዎችን  “በመኪና ጭኜ እቤት አስገባሁ፡፡” አለኝ፡፡

“አስገብተህ ምንአደረግከው??” ስለው፡-

“ለሰፈር ሰው በነጻ አከፋፈልኩና በምትኩ ፍቅር ገዛሁበት” አለኝ፡፡


2013 ጁን 27, ሐሙስ

ዕድሜው ከ18 ዓመት በታች ለሆነ ማንበብ ክልክል የሆነ ታሪክ

ኄኖክ ስጦታው

ልጅ እያለሁ የሰማኋቸው ተረቶች አስፈሪነት ያላቸው እና ከ18 ዓመት በታች ላለ ሰው እንዳይነገሩ መከልከል የሚገባቸው ነበሩ፡፡ የልጅነት አዕምሮዬ ከመዘገባቸው አስፈሪ ታሪኮች መካከል ዋንኛው “ቢሊጮ” ነው፡፡

“እኔ ቢሊጮ፣ ተንበላልጬ
የልጇን ስጋ፣ አበላሁ ልጬ…..!!!” (አበስኩ ገበርኩ!!!!)

/ቢሊጮ ብልጣብልጥ ልጅ ነው፡፡ የእንጀራ እናቱ ለሴት ልጇ “ዛሬ ቢሊጮን አጥበሽ፣ ቆዳውን ገፈሽ፣ ስጋውን ከትፈሽ ክሽን ያለ ምግብ ስሪልኝ” ብላ ወደገበያ ትወጣለች፡፡ ቢሊጮ ደግሞ የራሱን ብልጠት ተጠቅሞ የእንጀራ እናቱል ልጅ አጥቦና ቆዳዋን ገፎ ከሽኖ ፣…… ያበላታል፡፡/
እንደዚህ አይነት ተረቶች ይህም ዓለም በብልጣብልጦች እና ጨካኞች እንድትሞላ የራሳቸውን ሚና ይወስዳሉ፡፡  

እንደ “ቢሊጮ” አይነት ተረቶች ልጅን ለማነጽ ሳይሆን ለማፍረስ የሚነገሩ ለመሆናቸው አሌ የማይባል ሀቅ ቢሆንም ፋይዳቸው ግን ምንም ነበር፡፡

 አሁን ጊዜው ተለውጧል፡፡ ቢሊጮም ተረስቷል፡፡ ሆኖም ግን የቅርፅ ለውጥ እንጂ ይዘታቸው አንድ የሆኑ ፊልሞች ተበራክተዋል፡፡

በአስማት እና በጥንቆላ ላይ የተመሰረቱ ፊልሞች ቦታውን ይዘውታል፡፡ በአንድ ወቅት የአክሽን ፊልሞች “ቦንባርድ” የተሰኙ “ግሩፖች” በየመንደሩ እንዲፈለፈሉ ምክንያት እንደነበሩት ሁሉ አሁንም ትልቅ ስጋት ከፊታችን ተጋርጧል፡፡



በነካ እጄ ይቺን ሃሳብ ባክልስ¡?!¿
(/ለአዋቂ ተብለው የተሰሩና በየሲኒማ ቤት እየታዩ ያሉ ፊልሞችም አላጋጭ ትውልድ ቢፈጠር ተጠያቂ ናቸው!!!/)


2013 ጁን 23, እሑድ

ው-ዝ-ግ-ብ-ግ-ብ (ሌላው ገጽ) ---- ኄኖክ ስጦታው


----- ግብግብ ውስጥ እነሆ 1 ቅጠል

--
---
-----
---“ሩጫዬን ጨርሻለሁየሚሉት አይነት ጥቅሶች ያመራምሩኛል፡፡ ለምን መሰለህ በድንጋይ ድሪቶ እሱ ያላለውን መለጠፍህ ስለሚያሳዝነኝ ነው፡፡ የኔ ምርጥ አምላክ ሞተህ የተጻፈልህን የማንበቢያ ጊዜ የለውም፡፡ ሳትሞት የጻፍከውን ግን ሳይሰለች ያነብልሃል፡፡ ነው ትርጉሙ፡፡

ሩጫህን ለመጨረስ ሳትሮጥ ሞትህን መጠበቅ እንደሌለብህ እነግርሃለሁ፡፡ ባጭሩ ስንዝር በረጅሙ ሁለት እግርህን ተጠቅመህ የሮጥከው ሩጫ የፈጣሪን ልብ ለማራሪያነት አትጠቀም፡፡

ከሰሞኑ አንድ እናት ቂጣ ሰጡኛናነፍስ ይማር በልአሉኝ፡፡

የማንን?” አልኳቸው፡፡
የገድለ ገብርኤልንአሉኝ፡፡

ሀሳባቸው ገብቶኛል፡፡ የሟችን ክርስትና ስም እየነገሩኝ ነበር፡፡ እውነት ሆዴን ለመሙላት ስልይማር አይማርየማላውቀውን ነፍስ ለምን ልሸንግል?

መለስኩላቸው፡፡ ቂጣውን መለስኩላቸው፡፡

ምነው ልጄ?” አሉኝ፡፡

ነፍስ በስንዴ አትደለልም፡፡ ነፍስ በገንዘብ ኃይል አትፈታም፤ በቁጥር የጋገሩትን ቂጣበነፍስ ይማርሽንገላ ሆዳቸውን ለሚሞሉ አስመሳዮች ይስጡ፡፡አልኳቸው፡፡

ፊታቸው ከለበሱት ማቅ ጋር ሲመሳሰል አስተዋልኩ፡፡እኔ ነኝ እብዷ፡፡ ለእብድ መመፅወቴእያሉ ሄዱ፡፡ ትክክል ነበር የተናገሩት፡፡ ያለማስተዋል እብደትን ሊያጋቡብኝ አይችሉም፡፡

ቀባሪዬ፣ አርባ - ሰማንያ በሚል ስንክሳር ለመወጠር በዓመት - ሰባት ዓመት ዝክር፣ የቁርባን ክፍያ፣ በነፍስ ይማር ደፋ ቀና መፈታት መኖሩን አልነግርህም፡፡ አንተ በክፋት ጎዳና ያሰርካትን ነፍስ እራስህ እንድትፈታ እንጂ በቂጣና ሳንቲም ሽንገላይህን በልእንድትለኝ አልሻም፡፡

ለእኔ ገነትም ሲዖልም መሬት ነት፡፡ የመሬት እጅ የፈጣሪ እጅ ነው፡፡ እሳትም በረዶም ከመሬት ውጪ አይታየኝም፡፡ የኔ ፈጣሪ ጨካኝ አይደለም፡፡ ነፍስ ይማርቂጣ በተጀቦኑ ቃላት አይደለልም፡፡ በሬሳ ላይ ክምር የተጻፉ ጥቅስ ራርቶ ቀና ብለህ የምታየውን ሰማይ ከፍቶ ከጎኑ መቀመጥን አይቸርህም፡፡ ላንተ ከሰማይ በላይ ቤት እንዳለ ይታይሃል፡፡ ለእኔ ግን አይታየኝም፡፡ መሬት ግን ትታየኛለች፡፡ አንዴ የመኖር እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ከዚህ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜገነት - ሲዖልበሚባሉ ስፍራዎች አንገናኝም፡፡ ትልቁ ጽድቅና ለሰዎች ፍቅር መስጠት ነው፡፡ ምድራዊ ጽድቅና፡፡

ንብረቴ የምትለው ሁሉ የመሬት ንብረት ነው፡፡ ሃብቴ የምትለው መኮፈሻህ ከመሬት ውጪ የትም ሊሄድ አይችልም፡፡ አንተ እራስህ ከመሬት መኖርን እየተበደርክ ነው፡፡ ቁጥ-ቁጥ ብድርህን አንድ ጊዜ ትከፍላታለህ፡፡ ዕዳህን ሽሽት ከመሬት ልታመልጥ ከቶም ቢሆን አይቻልህም፡፡

ዛሬ ሕሊናዬ ገነትን ፈጥሮልኛል፡፡ አንተን ልጎዳ የማልፈልገው የሕሊናዬን ቅጣት ስለማልፈልግ ነው፡፡ ውስጤ እንዲነድ አልሻም፡፡ በመጠላለፍ ውጣውረድ የባዘነውን እግሬን ሞት ሲያቆመውሩጫዬን ጨረስኩብዬ መዘላበድ አልፈቅድም፡፡ሩጫውን ጨረሰእንድትለኝም አልፈልግም፡፡ ምድራዊ ሃብትህን እየለካህፍትሃ ቀብርየሚያስፈፅም ቄስ አታምጣብኝ፡፡ አንተ እራስህ ይህን ብቻ በለኝ፡- “አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለህአዎ!ያኔ መሬት ደስ ይላታል፡፡ ሀቁን አንተ እራስህ ታውቀዋለህ፡፡

ድንጋይ በዘመናት ዑደት ወደአፈር ይለወጣል፡፡ ብረት ከአፈር ወጥቶ በአፈር ይበላል፡፡ ዛፎች ከአፈር ተወልደው ወደ አፈር ይመለሳሉ፡፡ እንጨትን ብታከስለው እንኳን አመዱ አፈር ነውና፡፡ ተረዳኝ፡፡ ውሃ እንኳን በአየር ላይ ተንጠልጥሎ ሀይቅን አልፈጠረም፡፡ አንተ ግን ዓለምን የብስ እና ባህር ብለህ ትከፋፍላታለህ፡፡ ምድር ሽንቁር ባልዲ አይደለችም፡፡ ብትሆን ኖሮ ከባህሩ በታች መሬት መኖሩን ትረዳ ነበር፡፡


እኔ ብቻ አይደለሁም አፈሩ፡፡ ሁሉም ነገር አፈር ነው፡፡ የሰው አዕምሮ ከፈጠራቸው ፀረ-አፈር ነገሮች ውስጥ አንዱን ብትጠቅስልኝ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን ሁሉም ከመሬት ማሕፀን የተበዘበዙ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው መሬትን የምሻት፡፡ አፈር ነኝና ወደ አፈር መመለሴን እንድታዜምልኝ የምሻው፡፡ ......

ው-ዝ-ግ-ብ-ግ-ብ --- በ-ኄኖክ ስጦታው



((በመጽሐፍ መልክ ተዘጋጅቶ ከተቀመጠ ዓመታት ካለፉት ጽሑፎቼ አንዱ ላይ ቀንጭቤ ጋበዝኳችሁ፡፡፡፡፡))



…….እዛው መንገድ ላይ ነኝ፡፡ በመንደሬ መጋረጃ ጀርባ፤ ከጌጣጌጥ መሸጫ አብረቅራቂ ደጃፍ ስር፤ ከመንደሬ ጀርባ እገኛለሁ፡፡ አሁን በማልወደው የሰው ጫካ ውስጥ ቆሜያለሁ፡፡ የሕሊናዬ እውነታ ይታየኛል፡፡ በሰው ጫካ ውስጥ ብሆንም እታያለሁ፡፡ አላፊው አግዳሚው እርስ በርሱ ከሚተያየው የበለጠ እኔን ያያል፡፡ እያየም ያልፋል፡፡ ዳር መቆሜን መረዳት ችያለሁ፡፡ ውስጥ ሳይሆን ውጪ መሆን አለብኝ፡፡ ከሰዎች መሀል መሆን የምችል አይመስለኝም፡፡ ዳር ላይ ወጥቻለሁ -- ወይም -- መሀሉ ዳር ሆኗል፡፡

ባዶው እጄ ትከሻዬ ላይ ተንጠልጥሏል፡፡ ምንም ነገር አልያዝኩበትም፡፡ እግሮቼ ላይ እንደቆምኩ ቆሜያለሁ፡፡ ጭንቅላቴን የተሸከመውአንገቴ በትከሻዎቼ መሀል እንዳለ አለ፡፡ ከዚህ ውጪ መሆን ያለብኝን ሆንኩ እንጂ በተለየ የፍራቻ ዓይን እንድታይ የሚያደርግ ነገር የለኝም፡፡

አሁን ይበልጥ ከዳር ቆሜያለሁ፡፡ ቅድም ከነበርኩበት ግን ጋት ያህል ፈቅ አላልኩም፡፡ መንገድ ዘግቼ ይሆን? ሰፊ ቦታ ይታየኛል፡፡ በወዲያኛው ተቃራኒ የእግረኛ መንገድ ላይ ግን እግረኞች ይርመሰመሳሉ፡፡ እኔ ከቆምኩበት ቦታ ጋር እኩል መሆኑን አውቃለሁ፡፡ ለምን እንደጠበበም ግልፅ ነው፡፡ ሰዎች የሚጓዙት በወዲያኛው መንገድ ስለሆነ ጠበበ፡፡ ለምን እኔ በቆምኩበት መንገድ መጓዝ አቆሙ?

ሰዎች ወደበዙበት መንገድ ተሻግሬ ቆምኩ፡፡ ከምጠላው የሰው ጫካ መደባለቅ ፈልጌያለሁ፡፡ እንደፈለግኩት ሆነና መጀመሪያ ቆሜበት ወደነበረው ቦታ አሻግሬ ተመለከትኩ፡፡ በተቃራኒው በሰዎች ተጨናንቆ ታየኝ፡፡ አሁን የቆምኩበት ጠባብ መንገድ ደግሞ ሰፍቶኛል፡፡ ለምን እንደሰፋኝ ተረድቻለሁ፡፡ ብዙ ሰዎች እኔ በቆምኩበት ማለፍ አይፈልጉም፡፡ …….


ለምን??!! እኮ እኔ ማነኝ???!!!