2013 ጁን 27, ሐሙስ

ዕድሜው ከ18 ዓመት በታች ለሆነ ማንበብ ክልክል የሆነ ታሪክ

ኄኖክ ስጦታው

ልጅ እያለሁ የሰማኋቸው ተረቶች አስፈሪነት ያላቸው እና ከ18 ዓመት በታች ላለ ሰው እንዳይነገሩ መከልከል የሚገባቸው ነበሩ፡፡ የልጅነት አዕምሮዬ ከመዘገባቸው አስፈሪ ታሪኮች መካከል ዋንኛው “ቢሊጮ” ነው፡፡

“እኔ ቢሊጮ፣ ተንበላልጬ
የልጇን ስጋ፣ አበላሁ ልጬ…..!!!” (አበስኩ ገበርኩ!!!!)

/ቢሊጮ ብልጣብልጥ ልጅ ነው፡፡ የእንጀራ እናቱ ለሴት ልጇ “ዛሬ ቢሊጮን አጥበሽ፣ ቆዳውን ገፈሽ፣ ስጋውን ከትፈሽ ክሽን ያለ ምግብ ስሪልኝ” ብላ ወደገበያ ትወጣለች፡፡ ቢሊጮ ደግሞ የራሱን ብልጠት ተጠቅሞ የእንጀራ እናቱል ልጅ አጥቦና ቆዳዋን ገፎ ከሽኖ ፣…… ያበላታል፡፡/
እንደዚህ አይነት ተረቶች ይህም ዓለም በብልጣብልጦች እና ጨካኞች እንድትሞላ የራሳቸውን ሚና ይወስዳሉ፡፡  

እንደ “ቢሊጮ” አይነት ተረቶች ልጅን ለማነጽ ሳይሆን ለማፍረስ የሚነገሩ ለመሆናቸው አሌ የማይባል ሀቅ ቢሆንም ፋይዳቸው ግን ምንም ነበር፡፡

 አሁን ጊዜው ተለውጧል፡፡ ቢሊጮም ተረስቷል፡፡ ሆኖም ግን የቅርፅ ለውጥ እንጂ ይዘታቸው አንድ የሆኑ ፊልሞች ተበራክተዋል፡፡

በአስማት እና በጥንቆላ ላይ የተመሰረቱ ፊልሞች ቦታውን ይዘውታል፡፡ በአንድ ወቅት የአክሽን ፊልሞች “ቦንባርድ” የተሰኙ “ግሩፖች” በየመንደሩ እንዲፈለፈሉ ምክንያት እንደነበሩት ሁሉ አሁንም ትልቅ ስጋት ከፊታችን ተጋርጧል፡፡



በነካ እጄ ይቺን ሃሳብ ባክልስ¡?!¿
(/ለአዋቂ ተብለው የተሰሩና በየሲኒማ ቤት እየታዩ ያሉ ፊልሞችም አላጋጭ ትውልድ ቢፈጠር ተጠያቂ ናቸው!!!/)


ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ