2016 ዲሴምበር 23, ዓርብ

“ማሳ – ደግ”

(ኄኖክ ስጦታው)

በእንክርዳድ ማሳ ጥቂት ስንዴ በቅሎ
ይስፋፋ ጀመረ “እሕል ነው” ተብሎ።
*
ስንዴ ለሆድ ሲባል፣ በሰው መኮትኮቱ
ተነቅሎ ቢጣልም፣ እንክርዳድ ነው ብርቱ 
ሳይዘሩት ይበቅላል፣ የት ይሂድ ከርስቱ?!
*

ኮትኩቶ ማሳደግ፣ ቀልቦ ማደለብ፣ የሰው ታላቅ ዘዴ
“ ደረሰ… በሰለ…” የሚሉኝ በዙሳ ፣ ሊበሉኝ ነው እንዴ?!