2016 ማርች 9, ረቡዕ

ተነሳ ተራመድ - ኄኖክ ስጦታው ናኁሰናይ

ተነሳ ተራመድ
---------
"ተነሳ ተራመድ! ክንድህን አበርታ!
ላገር ብልፅግና ለወገን አለኝታ!!"
እምም…
*
መነሻችን መቼ ጠፋ?! ለመበልፀግ ስንገሰግስ
ተፈጥሮን ፊቷን አዞረች። እንዴት ወደኛ እንመልስ?!
*
"ተነሳ ተራመድ! ክንድህን አበርታ!
ላገር ብልፅግና ለወገን አለኝታ!!"
*
"ተፈጥሮ የግብአት ምንጭ፣ ተፈጥሮ የእድገት አለኝታ
ኢንዱስትሪ ነው መርሃችን፤ ድህነት ድባቅ ይመታ!!"
*
"ተነሳ ተራመድ! ክንድህን አበርታ!
ላገር ብልፅግና ለወገን አለኝታ!!"
*
የኃያላን ተሞክሮ ውጤት፣ የእድገት ጉዞ ትግበራ
ተፈጥሮን ሚዛን አስቶ፤ ለዜጎች ፍላጎት ሲሰራ
ዋስትና በገንዘብ ተለካ፤ ብልፅግና በሸቀጥ ተመራ…
ውራ የመሆን ጨዋታ፣ አይመራምና በጭራ…
ተቀበል!
*
"ተነሳ ተራመድ! ክንድህን አበርታ!
ላገር ብልፅግና ለወገን አለኝታ!!"
*
ወደፊት መጓዝ እንዳለው፤ ወደኋላም እንመለስ
ተፈጥሮን ማጥናት አይበቃም፣ ኗሪ ጎጆውን ሲቀልስ።
*
"ተነሳ ተራመድ!
ክንድህን አበርታ!
መጥረቢያ ነው ጠላትህ፣ አንተን በድርቅ የመታ!!!
"ተነሳ" ሲሉህ ተነሳ!
አምባገነን ነው ተፈጥሮ፣
"እንዳያልፉት የለም" ከማለት፤ የእልቂት ታሪክ ሞነጫጭሮ
ወደኋላ እንመለስ፣ እርቅ እንፍጠር ከተፈጥሮ
የደን ታሪክ ይሰራ፣ የደም ታሪክ ተሽሮ።
*
ተፈጥሮ ለጨቆኗት ጨቋኝ ነች፤ 
Sep 20, 2015 1:42:12 AM