2013 ጁን 23, እሑድ

ው-ዝ-ግ-ብ-ግ-ብ (ሌላው ገጽ) ---- ኄኖክ ስጦታው


----- ግብግብ ውስጥ እነሆ 1 ቅጠል

--
---
-----
---“ሩጫዬን ጨርሻለሁየሚሉት አይነት ጥቅሶች ያመራምሩኛል፡፡ ለምን መሰለህ በድንጋይ ድሪቶ እሱ ያላለውን መለጠፍህ ስለሚያሳዝነኝ ነው፡፡ የኔ ምርጥ አምላክ ሞተህ የተጻፈልህን የማንበቢያ ጊዜ የለውም፡፡ ሳትሞት የጻፍከውን ግን ሳይሰለች ያነብልሃል፡፡ ነው ትርጉሙ፡፡

ሩጫህን ለመጨረስ ሳትሮጥ ሞትህን መጠበቅ እንደሌለብህ እነግርሃለሁ፡፡ ባጭሩ ስንዝር በረጅሙ ሁለት እግርህን ተጠቅመህ የሮጥከው ሩጫ የፈጣሪን ልብ ለማራሪያነት አትጠቀም፡፡

ከሰሞኑ አንድ እናት ቂጣ ሰጡኛናነፍስ ይማር በልአሉኝ፡፡

የማንን?” አልኳቸው፡፡
የገድለ ገብርኤልንአሉኝ፡፡

ሀሳባቸው ገብቶኛል፡፡ የሟችን ክርስትና ስም እየነገሩኝ ነበር፡፡ እውነት ሆዴን ለመሙላት ስልይማር አይማርየማላውቀውን ነፍስ ለምን ልሸንግል?

መለስኩላቸው፡፡ ቂጣውን መለስኩላቸው፡፡

ምነው ልጄ?” አሉኝ፡፡

ነፍስ በስንዴ አትደለልም፡፡ ነፍስ በገንዘብ ኃይል አትፈታም፤ በቁጥር የጋገሩትን ቂጣበነፍስ ይማርሽንገላ ሆዳቸውን ለሚሞሉ አስመሳዮች ይስጡ፡፡አልኳቸው፡፡

ፊታቸው ከለበሱት ማቅ ጋር ሲመሳሰል አስተዋልኩ፡፡እኔ ነኝ እብዷ፡፡ ለእብድ መመፅወቴእያሉ ሄዱ፡፡ ትክክል ነበር የተናገሩት፡፡ ያለማስተዋል እብደትን ሊያጋቡብኝ አይችሉም፡፡

ቀባሪዬ፣ አርባ - ሰማንያ በሚል ስንክሳር ለመወጠር በዓመት - ሰባት ዓመት ዝክር፣ የቁርባን ክፍያ፣ በነፍስ ይማር ደፋ ቀና መፈታት መኖሩን አልነግርህም፡፡ አንተ በክፋት ጎዳና ያሰርካትን ነፍስ እራስህ እንድትፈታ እንጂ በቂጣና ሳንቲም ሽንገላይህን በልእንድትለኝ አልሻም፡፡

ለእኔ ገነትም ሲዖልም መሬት ነት፡፡ የመሬት እጅ የፈጣሪ እጅ ነው፡፡ እሳትም በረዶም ከመሬት ውጪ አይታየኝም፡፡ የኔ ፈጣሪ ጨካኝ አይደለም፡፡ ነፍስ ይማርቂጣ በተጀቦኑ ቃላት አይደለልም፡፡ በሬሳ ላይ ክምር የተጻፉ ጥቅስ ራርቶ ቀና ብለህ የምታየውን ሰማይ ከፍቶ ከጎኑ መቀመጥን አይቸርህም፡፡ ላንተ ከሰማይ በላይ ቤት እንዳለ ይታይሃል፡፡ ለእኔ ግን አይታየኝም፡፡ መሬት ግን ትታየኛለች፡፡ አንዴ የመኖር እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ከዚህ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜገነት - ሲዖልበሚባሉ ስፍራዎች አንገናኝም፡፡ ትልቁ ጽድቅና ለሰዎች ፍቅር መስጠት ነው፡፡ ምድራዊ ጽድቅና፡፡

ንብረቴ የምትለው ሁሉ የመሬት ንብረት ነው፡፡ ሃብቴ የምትለው መኮፈሻህ ከመሬት ውጪ የትም ሊሄድ አይችልም፡፡ አንተ እራስህ ከመሬት መኖርን እየተበደርክ ነው፡፡ ቁጥ-ቁጥ ብድርህን አንድ ጊዜ ትከፍላታለህ፡፡ ዕዳህን ሽሽት ከመሬት ልታመልጥ ከቶም ቢሆን አይቻልህም፡፡

ዛሬ ሕሊናዬ ገነትን ፈጥሮልኛል፡፡ አንተን ልጎዳ የማልፈልገው የሕሊናዬን ቅጣት ስለማልፈልግ ነው፡፡ ውስጤ እንዲነድ አልሻም፡፡ በመጠላለፍ ውጣውረድ የባዘነውን እግሬን ሞት ሲያቆመውሩጫዬን ጨረስኩብዬ መዘላበድ አልፈቅድም፡፡ሩጫውን ጨረሰእንድትለኝም አልፈልግም፡፡ ምድራዊ ሃብትህን እየለካህፍትሃ ቀብርየሚያስፈፅም ቄስ አታምጣብኝ፡፡ አንተ እራስህ ይህን ብቻ በለኝ፡- “አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለህአዎ!ያኔ መሬት ደስ ይላታል፡፡ ሀቁን አንተ እራስህ ታውቀዋለህ፡፡

ድንጋይ በዘመናት ዑደት ወደአፈር ይለወጣል፡፡ ብረት ከአፈር ወጥቶ በአፈር ይበላል፡፡ ዛፎች ከአፈር ተወልደው ወደ አፈር ይመለሳሉ፡፡ እንጨትን ብታከስለው እንኳን አመዱ አፈር ነውና፡፡ ተረዳኝ፡፡ ውሃ እንኳን በአየር ላይ ተንጠልጥሎ ሀይቅን አልፈጠረም፡፡ አንተ ግን ዓለምን የብስ እና ባህር ብለህ ትከፋፍላታለህ፡፡ ምድር ሽንቁር ባልዲ አይደለችም፡፡ ብትሆን ኖሮ ከባህሩ በታች መሬት መኖሩን ትረዳ ነበር፡፡


እኔ ብቻ አይደለሁም አፈሩ፡፡ ሁሉም ነገር አፈር ነው፡፡ የሰው አዕምሮ ከፈጠራቸው ፀረ-አፈር ነገሮች ውስጥ አንዱን ብትጠቅስልኝ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን ሁሉም ከመሬት ማሕፀን የተበዘበዙ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው መሬትን የምሻት፡፡ አፈር ነኝና ወደ አፈር መመለሴን እንድታዜምልኝ የምሻው፡፡ ......

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ