2012 ኖቬምበር 16, ዓርብ

ይኼ ልቤ . . . አልታወቀ - ሔርሜላ ትጽፋለች!!


ይኼ ልቤ . . . አልታወቀ
መቼ አምልጦ እንደመጣ
መቼስ አመል እንዳወጣ
ቤትህ ደርሶ - ደጅ አንኳኩቶ
ሳይታሰብ - አፀድህን ዘልቆ ገብቶ
ሳይጠራ - ከእልፍኝህ ተሰይሞ
ሳይጋበዝ - ከማዕድህ ታድሞ
ሳይታይ - አብሮህ ከዋለ ካደረ
እኔን ትቶ ካንተ መኖር ከጀመረ
ሰ - ነ - በ - ተ
ግና . . . ተግባር እንደል'ም አልቀለለ
እግሬ ልቤን መች ተከተለ
ከደሳሳ ጎጆዬ በራፍ ቆሜ (በሙሉ ዓይኔ እንኳ ሳልደፍር)
የኮራ አፀድህን ሳይ አግድሜ
ዓይኖቼ ሊያዩህ እንደናፈቁ
ጣቶችህ ከእጆቼ እንደ'ልም እንደራቁ
ምን አለብህ . . . በኮራ የንጉስ ርምጃህ
በመንደሩ ተንጎማልለህ
የኔ እግር ብርክ ሳይታይህ
እንደዋዛ ታልፈኛለህ . . .
ባለሹመት አጀበ ብዙ
ገደብ የለሽ ዓለም ደርዙ
ቢያነቅፍህ 'ልነጠፍ' ባይ የማታጣ
መካችህ ብዙ ቢያጋጥምህ የሚቃጣ
እና ለምን . . . እንዴት ተብሎ
ዓይንህ ወደኔ 'ሚያይ አሽቆልቁሎ
ቊንዳላህ ቢፈተሸ - ቢመረመር ቆዳህ
የቆነጃጅት ቃል - ድሪ ጌጣጌጥህ
ዓይናቸው መዋያህ - ልባቸው ማደሪያህ
ታዲያ ማን ከአጀቡ ነጥሎ
ከዙሪያህ የዓይን አዋጁን አግልሎ
ያመላክትህ ክሳይ መልኬን
ባይንህ ያግባ ልጥፍ ዳሴን?
የኔን ዓለም ሞልተህ - መውጣትህ መንጋቱ
ሲሆንልኝ ኖረ - መግባትህ መምሸቱ
ባታስተውለኝም በዓለምህ ባልታይ
ከቤቴም ባይሞላ አዱኛ ወ ሲሳይ
ይህንን አውቃለሁ . . .
ንጉስ ከእረኚት ጋር - በፍቅር ወደቀ
መደምደሚያው ሆና - ሌላ ውበት ናቀ
ስለዚህ . . . እንዲህ ነው ጸሎቴ
ባጠገቤ ስታልፍ አንድ ናት መሻቴ
እንቅፋት በመታህ - በጣለህ ከእርሻዬ
ክፉኛ አንሸራቶህ - ውደቅ ከማሳዬ
ላንዲት ደቂቃ እንኳ - መኖሬን እንድታውቅ
ቁስልህን ለማከም - ኖራለሁ ስናፍቅ
June 2011


Hermy Writes

2 አስተያየቶች:

  1. yayn fikir kfu new.ayinagerut neger firhat;aydebqut neger wey chinq.sew yashawun mafqer yichilal yigebawalim.sew hulu yafeqerewun yagegnal malet gin aydelem beteley yal'acha endehon.sifsif yemtaderg gitim nech....endezih hogne yasalefkutn zemen yastawusegnal.ej yibarkilin

    ምላሽ ይስጡሰርዝ