2013 ጁላይ 15, ሰኞ

“የፒያሳ አመልህን ይዘህ ቦሌ አትሂድ” - ኄኖክ ስጦታው



ወደ ቦሌ አካባቢ ሄደህ ፣ መዝናናት ካማረህ እባክህን ከማጨብጨብ ተቆጠብ፡፡

ከእለታት በአንድ የተረገመች ቀን እንዲህ ሆንኩላችሁ፡፡ ደምበል አካባቢ ካለው “ላ ፓራዚያን ካፌ” እግር ጥሎኝ ገባሁ፡፡ ከውስጥ መግባት ፈርቼ ወይም ሸሽቼ ከበረንዳው በስተቀኝ ወዳለችው የመናፈሻ ሳምፕል ወደመሰለችኝ “መናፈሻ” ገብቼ ተቀመጥኩ፡፡ ለደቂቃዎች ዞር ብሎ የሚያየኝ አስተናጋጅ አጣሁና በጭብጨባ ለመጥራት እጄን ማፋተግ ጀመርኩ፡፡ ያው …. ፒያሳ የለመደብኝ አመሌ አገረሸ፡፡

/ፒያሳ እኮ ካላጨበጨብክ የሚታዘዝህ አስተናጋጅ ጥቂት ነው፡፡ ኧረ አንዳንዴማ፣ አስተናጋጅ ለመጥራት ልታፏጭ ሁሉ ትችላለህ፡፡ የምመክርህ ነገር ቢኖር የፒያሳ አመልህን ይዘህ ቦሌ አትሂድ ፡፡/

ይህ አመሌ አገሸና ማጨብጨብ ጀመርኩ፡፡ አጨበጨብኩ፡፡ ዝም!
ደጋግሜ አጨበጨብኩ፡፡ ጭጭ!

የጭብጨባዬ ድምጽ “ላውድ” ላይ አድርጌ ቀወጥኩት፡፡ አሁን ዘዴዬ ሠራ መሰል አንዲት አስተናጋጅ መጣችና ቁልቁል በመመልከት “ምን ይጠበስ?!?” በሚል አስተያየት ታየኝ ጀመር፡፡

“ምንድን ነው?! ሳጨበጭብ አትሰሙም እንዴ!??!” አልኩ ቁጣ ባጠቃው ድምፀት፡፡

“ይኸው ልጨፍር መጣሁ እኮ!!” አለች እጆቿን ወገቧ ላይ አድርጋ፣ ትከሻዋንም “እስከስ” እያደረገች፡፡

ኧረ፣ መውረግረግ!!!


ምነው እጄን በቆረጠው! ምነው አቅሜን አውቄ እዛው ፒያሳ ባጨበጭብ!! ሃሃሃ /ባላጨበጭብስ/

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ