ሰኞ 21 ጃንዋሪ 2013

ጌታው ባለህበት - ማረፍ በቀለ













ጌታው ባለህበት

አጋድመህ መዘንጠል ከለመድክበቱ
የሚታረድ ጠቦት ከምታስስበት
እዛው ካክራሞትህ ከበረት ከጋጡ
በሩን ተሸሽገህ በጥጋት ቀዳዳ
በሽንቁሩ አልፈው የሚጉረጠረጡ
እነዛ አይኖችህ ጨለማ ይሁኑ!
አልልህም እኔ
ድብስብስ ለሊትን የጭርታን ጊዜ
የዝለትን ሰበብ የቀንን ድንጋዜ
ብርታቱ አድርጎ የሚጣራ ድምፅህ
ዜማ እያምታታ
የእረኛውን ዋሽንት አምስሎ እየመታ
የሚያፏጭ ልሳንህ
ዘላለም ይደፈን ጎሮሮህ ይዘጋ!
አልልህም እኔ
ድንቃፍ ላይመልሱ ላያስጥሉ ከውርጭ
ጨብጠው ላይመሩ ረብ ላይሰጡ ቅንጣት
እቅፍ የዘረጉ - ምርኩዝ ቢያድርጓቸው ሰልትው የተዋጉ
ነፍስ ድረስ ዘልቀው ነፍስ ያስመረቀዙ
እነዚያ እጆችህ አመል የለመዱ
ሰይፍ ይረፍባቸው በጦር ይቀደዱ
አልልህም እኔ

ቅዳሜ 19 ጃንዋሪ 2013

ቅዥት - ሄኖክ ስጦታው




ቅዥት

የህልም ዓለምን ሳካልል፣
በቁም ሳለሁ ተኝቼ
ከወደቅሁበት ፀሊም ዓለም፣
ሳልፈልገው ተገፍቼ፤
እንደ ሌሊቱ ቅዥቴ፣ መሮጥ ተስኖት እግሬ
ሳልፈልገው ተተብትቤ፣ እግር-ተወርች ታስሬ፤
ልክ እንደዚያው ቅዥቴ፣
በቁም ታፍኖ አንደበቴ
እንዳላመልጥ ከእስራቴ፣
በኖ ጠፋና ብርታቴ . . .

ዘመኔን በግድ ታቅፌ
በቃ እንዳልል ጋት አልፌ
ተወግቼ አንዳች መርፌ፤

ተውሰብስቤ በእልፍ ቅዥት
ስንቱን ዓለም አካለልኩት?!
መሬት ለመሬት ስንፏቀቅ፣
ሰማየ-ሰማያት ስንሳፈፍ
ድንገት መጋለብ ጀምሬ፣
ድንገት ባሕር ስቀዝፍ . . .
ስንቱን ዓለም አካለልኩት?!

የማላውቀው ፤ ግን ያየሁት
የምኖረው፤ ግን ያከልሆንኩት
የማፈቅረው፤ ግን ያጣሁት፤
የምመኘው፤ ግን ያልሆንኩት. . . !

ትላንት ቅዥት፣ ዛሬ ቅዥት
መዋል ቅዥት፤ ማደር ቅዥት፤ መኖር ቅዥት፣
ያሻሁትን ብቃዠውም፤
ቅዥቴን ግን አልኖረውም
የኖርኩትን አልቃዠውም!

መጋቢት፣ 28፣ 1999ዓ.ም
ሄኖክ ስጦታው ከ(ሀ-ሞት የግጥም ስብስብ መጽሐፍ፣ በቅርብ ቀን የሚወጣ)

ሐሙስ 17 ጃንዋሪ 2013

ሐዘንሽ አመመኝ/ ደበበ ሰይፉ















ውል አልነበረንም የፍቅር ቀጠሮ
ቃልም አላኖርንም በወግ ተቀምሮ፤
እኔ አንቺን እንዳላይ
አንቺ እኔን እንዳታይ አምባችን ተቃጽሮ
ዕጣችን ተካሮ፤
ቀለምሽ ከዐይኔ አሻራሽ ከጣቴ ባይጠፋ ተማትሮ
(እትብት እምብርት ሁኖ እንዲኖር ደድሮ)
ይኸው አካሄደን በድንገት ዘንድሮ።
የገጽሽ ብርሃን ቢጠይም ፀዳሉ
ድምፅሽ ቢቀጥንብኝ ቢሠልብኝ ቃሉ
ወዘናሽ ቢማስን ዛሬ ያለውሉ
በእጆችሽ ጨበጠኝ ሐዘንሽ ሥዕሉ
ሐዘንሽ አመመኝ
ብሶትሽ ጠቀሰኝ።

እኔ እወድሻለሁ /ገብረክርስቶስ ደስታ /



















ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚሊዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንችን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ።
እኔ እወድሻለሁ
የሰማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ፅጌ-ረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደ ሎሚ ሽታ፡፡
እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
እኔ እወድሻለሁ፣
አበባ እንዳየ ንብ፡፡

እሑድ 13 ጃንዋሪ 2013

ይድረስ ለወንድሜ ለማላውቅህ (ባለቅኔ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅን)




ይድረስ ላንተ ለማላውቅህ
ለወንድሜ ሩቅ ለማልፍህ
ለምታውቀኝ-ለማላውቅህ፥ ለምታየኝ-ለማላይህ. . .
ማነህ ባክህ?
ሳትወደኝም ሳታምነኝም፥ አጢነህ ለምትፈራኝ
ስናገርህ አጠንቅረህ፥ አተኩረህ ለምትሰማኝ....
ይድረስ ለክቡር ወንድሜ፥ ለአረህ ዟሪው ለገታሩ
ለሩቅ ገጠሬ ነባሩ
ለማላውቅህ ለዳር ዳሩ፥....
ማነህ

ቅዳሜ 12 ጃንዋሪ 2013

ወንድ ብቻውን ነው እሚያለቅስ- ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን



ከወዳጅ ከዘመድ ርቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ      
ተሸሽጎ ተገልሎ፥ ተሸማቆ ተሸምቆ
ከቤተ-ሰው ተደብቆ
መሽቶ፥ የማታ ማታ ነው፥ ሌት ነው የወንድ ልጅ እንባው
ብቻውን ነው የሚፈታው፡፡ . . .
ብቻውን ነው የሚረታው፡፡ . . .
ችሎ፥ ውጦ፥ ተጨብጦ፥ ተማምጦ ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተወጥሮ
እንደደመና ተቋጥሮ
እውስጥ አንጀቱ ተቀብሮ . . .
መሽቶ፥ ረፍዶ፥ ጀምበር ጠልቆ
የጨለማ ድባብ ወድቆ
በእንቅልፍ ጥላ ሲከበብ፥ በዝምታ ሲዋጥ አገር
ፍጡር ሁሉ ተስለምልሞ፥ ብቸኝነት ብቻ ሲቀር . . .

ሐሙስ 10 ጃንዋሪ 2013

እግር እንይ! (ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን)


poem in pdf
እግር እንይ!
(ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን)

አርቀን ማስተዋል ማለት፣ የኛን ሥልጣኔ ድልድይ
እግር ማየት ነው ብለዋል፣ እስቲ እንግዲህ እግር እንይ!
            ያባቶችህ ያይን ድንበር፣ ከተረከዘ ሎሚ ሳያልፍ
            አንተ ግን ጆቢራው-ዘራፍ
ጠፍር አይወስንህ ጉብል
ጥሎ በዘመንህ ዕድል
ዓይንህ ባት አልፎ እንዲዋልል፤
ቴህ ወዲያ ጀግንነት የለ፣ ተዚህ የከረረ ግዳጅ
ባደባባይ የዱር ገደል፣ ስትናደፍ የእግር አዋጅ
ሌሊቱን በየሌት- ‘ግለብ’፣ ቀኑን ጭምር በጠራራ

ሰኞ 7 ጃንዋሪ 2013

አደፍርስ - የብዕር ጠብታ /ከባለፈው የቀጠለ/



ሙሉውን ለማንበብ
አደፍርስ - የብዕር ጠብታ 

(ከባለፈው የቀጠለ)

ቅንጣቢ ዳሰሳ ፡-ሄኖክ ስጦታው

              ****** ******      ****** *****

አደፍርስ የብዕር ጠብታ ነው፡፡ የጥበብ መታያ - የእውነት መገለጫ ነው፡፡ ድብቅ ሰብእና የለውም፡፡ የገፀ-ባህሪው ውስጠ ምስል ግልፅነት የተከተለ ነው፡፡ የአገራችን ደራሲያን ለዋና ገፀባህሪይ ነፃነት ለመስጠት የሚጠቀሙበት ተመሳሳይ የአሳሳል ስልት በአደፍርስ ላይ መስተወሉን ልብ ይለዋል፡፡

“ቀልድ ጨዋታ የማላዘወትር፣ የተሰማኝን ሃሳብ ያስቀይማል አያስቀይምም ብዬ ሳላስብ ቀጥታ መግለፅ የምወድ…” ገፅ129 እያለ እራሱን የገልጸዋል፡፡ ከደራሲው አንፃር ስለ አደፍርስ ግልፅ ባህርይ  የነገረናል፤ “የማይቦዝን ፣ ስለውጤቱም እምብዛም የማያስብ፣ እንደልቡ የሚናገር፤ ተቃዋሚዎቹም ከራስ ፀጉሩ የበዙ ናቸው…”
ዳኛቸው ወርቁ ለአደፍርስ እንደልቡ የመናገር ነፃነትን በመስጠት፣ የራሱን ነፃነት እንዳወጀ እናስተውላለን፡፡ እውነታውም ይህ ነበር፡፡ የወቅቱን ስርአት፣ ስርአቱ ለዘመናት የፈጠረውን ተፅዕኖ፣ ጭቆና እና ብዝበዛ ብሎም አጉል ልማዶችን በአደፍርስ አማከኝነት አውግዟል፡፡ በደራሲው ውስጥ አደፍርስ አለ፤ በአደፍርስ ውስጠም ደራሲው ፡፡

መጽሐፉ፣ በተማረው እና ባልተማረው ማህበረሰብ መሀል ለውን ለውጥ ያሳያል፡፡ ስለመሀይምነት መጥፋት ያትታል፡፡ አደፍርስ ለኢትዮጵያ  ያለውን ብሩህ ተስፋ ትምህርትን አስታኮ ይናገራል፡፡ መዕራፍ 26 ለዚህ ዋቢ የሚሆን ነው፡፡ የምዕራፉ ውይይት አደፍርስ በመጨረሻዎቹ ምዕራፍ ለያዘው ሥራ መጠቆሚያም ጭምር ሆኗል፡፡

“ሀዲስ” እና “አደፍርስ”   

አደፍርስ በዓሉ ግርማ የደረሰው “ሀዲስ” ረጅም ልብ ወለድ ዋና ገፀ ባህርይ ሀዲስ  ላይም  የባህርይ ተፅዕኖ ያሳደረ