(ኄኖክ ስጦታው)
በእንክርዳድ ማሳ ጥቂት ስንዴ በቅሎ
ይስፋፋ ጀመረ “እሕል ነው” ተብሎ።
*
ስንዴ ለሆድ ሲባል፣ በሰው መኮትኮቱ
ተነቅሎ ቢጣልም፣ እንክርዳድ ነው ብርቱ
ሳይዘሩት ይበቅላል፣ የት ይሂድ ከርስቱ?!
*
ኮትኩቶ ማሳደግ፣ ቀልቦ ማደለብ፣ የሰው ታላቅ ዘዴ
“ ደረሰ… በሰለ…” የሚሉኝ በዙሳ ፣ ሊበሉኝ ነው እንዴ?!
(ኄኖክ ስጦታው)
በእንክርዳድ ማሳ ጥቂት ስንዴ በቅሎ
ይስፋፋ ጀመረ “እሕል ነው” ተብሎ።
*
ስንዴ ለሆድ ሲባል፣ በሰው መኮትኮቱ
ተነቅሎ ቢጣልም፣ እንክርዳድ ነው ብርቱ
ሳይዘሩት ይበቅላል፣ የት ይሂድ ከርስቱ?!
*
ኮትኩቶ ማሳደግ፣ ቀልቦ ማደለብ፣ የሰው ታላቅ ዘዴ
“ ደረሰ… በሰለ…” የሚሉኝ በዙሳ ፣ ሊበሉኝ ነው እንዴ?!
(ኄኖክ ስጦታው ናኁሰናይ)
“ነበር” ላይ ሊያበቃ፣ የ“ነው” ባይ አቅጣጫ፤
ከ"ነው" እና "ነበር"፣ የታል የኔ ምርጫ?
•
መድረሻው መነሻ
መነሻው መድረሻ
ጠይቅ “የታል” ብለህ… “የታል ውጣ—ውረድ”?
(ሕይወት መሰላል ነው፤ የእርብራብ መንገድ!)
•
የጥያቄ ምላሽ፣ በምጥ ላይወለድ
“እውነት” ካስጨነቀህ፣
በስንዝር ቦታ ላይ፣ ጋት ጨምር… ተራመድ
መልሱን ተወውና፣ መጠየቅን ውደድ
ውጣ
ወይም
ውረድ!
ወጣ ያሉ የግዕዝ ቅኔያት
በአጋጣሚ አግኝቼ ያነበብኩት መጽሐፍ ነው። “ቅኔያዊ የእውቀት ፈጠራ“ ይሰኛል ርዕሱ። በማርዬ ይግዛው ተሰናድቶ በ የጀርመን የባህል ማዕከል፣ 2006 ዓ.ም የታተመ ነው።
“…አብዛኛዎቻችን ቅኔ ኃይማኖታዊነት ብቻ የሚንጸባረቅበት ይመስለን ይሆናል። ቅኔ የማይዳስሰው ነገር የለም። የጾታ ተራክቦን (የግብረ—ሥጋ ግንኙነትን) እና መዳራትን ጨምሮ።…” እያለ ይቀጥላል የመጽሐፉ ትንታኔ።
ቀነጫጭቤ ጋበዝኳችሁ፦
ቅኔ ፩
ኢይጠፍእ ሕልጽ እሳት ላዕሉ ወታህቱ፣
እስኪት ጉልጥምት እስመ ተዳፈነ ቦቱ።
ትርጉም፦
እምስ የላይና የታቹ እሳት አይጠፋም፤
ቁላ/ጉልጭማ (እንጨት) ተዳፍኖበታልና።
ምስጢር ፦
ጉልጭማ የተዳፈነበት እሳት እንደማይጠፋ ቁላ የሚገባበት እምስም ሙቀት አይለየውም። በተለምዶ እሳት የሚጠፋው በውሃ፣ ሙቀት የሚበርደውም በቀዝቃዛ ነገር ነው። እምስ ግን ራሱ የቁላን ትኩሳት የሚያስታግሰው በማይጠፋ ሙቀት ነው እንጂ ከቀዘቀዘ አስተናጋጅነቱ ይቀራል።
እሳቱ/ሙቀቱ የማይጠፋ የሚለው የመራባት የሰው እንስሳዊ ህይወት ምንጭ መሆኑንም ያመላክታልና በዚህ ግልፅ ወሲባዊ ቅኔ ውስጥም ስለ ሕይወት ቁም ነገር አልጣበትም።
ቅኔ ፪
እታገኝ ደመርኪ እምላእለ ክብርኪ ክብር፣
ለነዳይ እስኪት እስመ ወሀብኪ ቂንጥር።
ትርጉም ፦
እታገኝ በክብር ላይ ክብር ጨመርሽ
ለድሃው ሰው ቁላ ብልት በመጽውተሽ። (መጽውተሽዋልና)
ምስጢር ፦
ይህ ቅኔ እማሆይ ገላነሽ እታገኝ የተባለች ልጃቸው ስታገባ የተቀኙት ነው ይባላል። ሰሙ በዚህ ዓለም ለተራቡ ሰዎች የሥጋ ብልት ሳይቀር የሚመጸውቱ ሰዎችን ይገልፃል። ባለቅኔዋ እታገኝ የተባለችው ልጅ ስታገባ ለተራበ ቁላ የሚገባውን ምግብ በመስጠት የጽድቅ ሥራ ማድረጓን አስመስጥረዋል።