2016 ፌብሩዋሪ 20, ቅዳሜ

ዝሆን ለምን…!?

(ኄኖክ ስጦታው ናኁሰናይ)

"የተረገመ ዝሆን!!" አለ በሃዘን ልቡ ተነክቶ። "በቃ፣ ለመቅበሪያ ጉድጓድ ለመቆፈር ተጨማሪ ቀን እዚህ ላድር ነው" ሲል አሰበ።
*
*
*
*
*
("በድሮ በድሮ" ጃሉድ ስታይል) ስንቀይረው
*
*

"የተረገመ ዝሆን!!" ሲል በብስጭት አጉተመተመ ጉንዳኑ። "በቃ፣ አፈር ከሚበላው ተሸክሜ ብወስደውና ብንበላው ይሻላል" 
*
*
(ሞት አደላድሎ አፈር ካልተጫነኝ፣ 
ቃሌን አላጥፈውም ካንተ ጋ ኗሪ ነኝ።) 
*
*
ጉንዳኑ ሐዘን ልቡን አደማው።

እናም እውነታውን እያሰበ እንዲህ አለ…
"የተረገመ ዝሆን!! በፍቅር ላሳለፍኩት አንድ ሌሊት ስል እድሜዬን ሙሉ መቃብሩን ልቆፍር ነው ማለት ነው" 
*
*
*
በመቀጠልም ዝሆኑ ሃውልት ላይ የሚያሰፍረው አጭር ግጥም አዘጋጀ፦

"ለምን ሞተ ቢሉ 
ንገሩ ለሁሉ ሳትደብቁ ከቶ
ከዘመን ተኳርፎ፣ ዘመን ተጣልቶ"

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ