2016 ፌብሩዋሪ 19, ዓርብ

ተራማጅ እሳቤ ፵፯

( ኄኖክ ሥጦታው ናኁሰናይ )

ውሃ…
*
ከፍታን መርጦ ሲጣበቅ፣ በረዶ ሆኖ ሲደድር
ውሃም ይወጣል ዳገት፣ ይወርዳል ሙቀቱ ሲንር።
*
በረዶ አቅላጩ ሙቀት፣ በድን አካል ካፈረሰ
ነዲድ ያገኘው አለት፣ ቀልጦ ቁልቁል ከፈሰሰ
መጠጠርስ እንደውሃ ፣
መቅለጥ …
መትነን…፣
 ሽቅብ መውጣት… ቁልቁል መውረድ…
(ቅዝቃዜ ፅሞና ነው። ርጋታን ለአፍታ ልውደድ)
ራስ…
ለራስ…
ከራስ…  ጋ
ጠምቶኛል ዘልቆ መዋኻድ
ከመትነን ከፍታ በታች፦
እንደበረዶ ጠጥሮ፣ ደግሞ እንደ ዥረት ለመውረድ።
*
ውሃ…
ወንዙ መንገድ ቀይሯል፣ የድርቅ ዱካውን ትቶ
ወዴት ወርዶ አለቀ? ከምድር ሰርጎ ገብቶ?
በሰማይ መንገዱ ተጓዘ? በትነት ሽቅብ ወጥቶ?
*
ራሴን ተጠማሁ…

በደረቀው መንገድ ላይ፣ ቆሜ ነበር ሃሳብ ጠምቶኝ
አሁን አቅጣጫው ሲገባኝ፣ የወንዙን መንገድ መረጥኩኝ
ወደሄደበት ብሄድ ነው፤ ጥቂት ውሃ የማገኝ።

ጠምቶኛል…

1 አስተያየት: