2013 ጁን 10, ሰኞ

“ነወር”፣ “ነውረኛ”፣ “ነዋሪ” - ኄኖክ ስጦታው

“ነወር”
“ነውረኛ”
“ነዋሪ” 
-
-
-
-

“ነወረ” ማለት . . . “አነወረ፣ አስነወረ፣ አሳፈረ፣ ነውረኛን አደረገ፣ ወይም ተነወረ፣ በነውር ነገር ተከሰሰ” ይለዋል ከሳቴ ብርሃን የአማርኛ መዝገበ ቃላት ፤ በተሰማ ሀብተ ሚካኤል ግጽው የተዘጋጀው፡፡ 

“ነውረኛን” ማለትን ሲፈታው ደግሞ፡- “ነውርን የተመላ፣ ነውርን ከመስራት የማያርፍ(ተነወረ፣ ነውረኛ ሆነ) ” 

“ነዋሪ” ማነው? ካላችሁ . . መልሱ. . . አንድም በመንግስቱ ኅልፈት ጥፋት የሌለበት፣ ሳይለዋወጥ ፣ ጊዜ ሳይወስነው የሚኖር አምላክ ነው፡፡ ሌላም፣ በሕይወት ሥጋ የሚኖር፣ ከቦታው የማይላወስ…. ባለበት ጠንቶ የሚኖር ነው፡፡ ስለዚህም ነው መሰል፣ “ነወር” ስንባል ፣ በተለምዶ “በእግዜር” እንላለን፡፡ 

አሁን አሁን እየተስተዋሉ ያሉት እውነታዎች ስንገመግም አንድ ትልቅ ቁም ነገር ትርጉም አልባ እየሆነ ለመሆኑ ማስረጃ መጥቀስ የማያሻው ጉዳይ ነው፡፡ በማሕበረሰቡ ድንጋጌ (ይህ ድንጋጌ በነዋሪዎች ቅቡልነት /ተለምዷዊ ስምምነት/ አቋም የያዘ ነጥብ ፤ በአብላጫው ተቀባይነት ድምፅ የፀደቀ፡፡) ? 

“ነወር” የሚለውን ቃል ስንበረብረው “ኖር” ከሚለው ቃል በተጨማሪ “ነውር” የሚል ተጻራሪ ፍቺ አቅፏል፡፡ /እንግዲህ እኔ እንደተረዳሁት ነው ትንታኔው/ . . . አንድም ለክብር አንድም ለተግሳጽ የምንጠቀምበት ይህ ባህል ከመጥፋት እንታደገው!

ኄኖክ ስጦታው

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ