2012 ጁላይ 19, ሐሙስ

እማሆይ ገላነሽ አዲስ ማን ናቸው?



እማሆይ ገላነሽ አዲስ_፲፰፻፹፱᎗፲፱፻፸፰ ስለ አንዲት ስመ-ጥሩ ኢትዮጵያዊት መምህርትና ባለ ቅኔ ታሪክና ማንነት ስናስታውስ ‘ጽላሎ ይበልጣል አንቺ ያለሽበቱ‘ የተባለላቸውንና ሣር ቅጠሉ አድናቆቱ የቸራቸውን እማሆይ ገላነሽ አዲስን ከጽላሎ አማኑኤል ሳናነሳ አናልፍም።

ከቄስ ገበዝ ሐዲስ ኪዳናትና ከወ/ሮ ወርቅነሽ እንግዳ በምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት በይልማና ዴንሳ ወረዳ በሚገኘው ደብረ ጽላሎ አማኑኤል በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም ተወለዱ። በእናት አባታቸው ቤትም በንክብካቤ አደጉ። አባታቸው የሚያስተምሩትንም ቅኔ ሥራዬ ብለው ይከታተሉ ነበር።

የስምንት ዓመት ልጅ እያሉ አንድ ቀን ከእናታቸው ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሄዳሉ። በሴቶች መቆሚያ ከእናታቸው ፊት ተቀምጠው እንዳሉ በዚያው ቤተ ክርስቲያን የሚያገለግሉት ከሥርዓተ ቅዳሴው በኋላ ቅኔ ይዘርፋሉ።

“በታቦርሂ አመ ቀነጸ መለኮትከ ፈረስ” ማለትም መለኮትህ ፈረሰ በደብረ ታቦር ተራራ በዘለለ ጊዜ ብለው ቄስ ገበዝ ለዓለሙን ሲጀምሩ፡ ገላነሽ ሐዲስ ባልታሰበና ባልተጠበቀ ሁኔታ ከተቀመጡበት ተነሥተው “ኢክሀሉ ስሂቦቶ ሙሴ ወኤልያስ” አሉና ነጥቀው እርፍ። ትርጉሙም ሙሴና ኤልያስ ሊስቡት አልቻሉም ብለው አባታቸውን በጉባኤ መካከል ነጥቀዋቸው መወድሱን ጨርሰውታል። አባታቸውም እዚያው ጉባኤ መካከል አዚምላት በማለት ተናግረዋል ይባላል። በኋላም መልሰው እንዲህ አሏቸው፡ “ወእንዘ ትትናገሪ ዘንተ በአድንኖ ክሳድ ወርእስ በከመ አነ ስማዕኩክ ኢይሰማዕኪ ጳውሎስ።“

ይህ ጳውሎስ በመልእክቱ ሴቶች በጉባኤ መካከል ገብተው እንዳያስተምሩ የተናገረውን ቃል በማስታወስ እኔ እንደ ሰማሁሽ ይህንን ስትናገሪ ጳውሎስ እንዳይሰማሽ ለማለት ነው።

ከዚህ በኋላ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የተሰባሰቡት ሊቃውንትና ሕዝብ ይህ ምስጢር እንደተገለጸላቸው ባዩ ጊዜ፤ በሁኔታው በመገረምና በመደነቅ ካህናቱ በወረብ፥ ጎበዛዝቱ በሆታ ሴቱ በእልልታ ገላነሽን እያመሰገኑ መንገድ ጀመሩ። እንደ ንግሥት ጉዞ በአልጋ ሆነው መጋረጃ ተጋርዶላቸው እቤታቸው ደረሱ። ሕዝቡም ከፍ ያለ የደስታ ግብዣ አድርጎ ሰነበተ።

          ይህ ደስታ ብዙም ሳይቆይና ስሜቱ ሳይደበዝዝ ገላነሽ ሕይወት ላይ አስደንጋጭ ክስተት ተፈጠረ። በለጋ ዕድሜያቸው