2014 ሜይ 14, ረቡዕ

የበርሃ አንበጣ - አማራጩ የምግብ ግብዓት


በኄኖክ ስጦታው

ዛሬ የሰፈራችን ሕፃናት ሰማዩን ከወረሩት አንበጣዎች በላይም መነጋገሪያ ለመሆን በቅተዋል፡፡ (“አንበጣ ናቡና ጠጣ . . . ” እያሉ ለመጀመሪያ ጊዜበአማርኛሲዘምሩ ተሰምተዋል፡፡ ከዚህም በላይ፣ አንገብጋቢው የስኳር እጥረት ችግርን አስመልክተው እሪታቸውን አሰምተዋል፡፡) በነገራችን ላይ፣ ከዚህ መዝሙር ውስጥ አንድ ስንኝ ይገርመኛል፡፡ስኳር የለኝም እንዳትቆጣ...” ጥንትም የስኳር ችግር ነበር፤ ዛሬም እንዲሁ፡፡ (ማን ያውቃል¡ ግንባታ ላይ ያሉት - በለስ፣ ተንዳሆ፣ ኩራዝ፣ ወልቃይት. . . ስኳር ፋብሪካዎች ሥራ ሲጀምሩ መዝሙሩ ይለወጥ ይሆናል፡፡)

አንበጣ

የሰው ልጆች፣ አማራጭ ነፍሳትን በመመገብ የምግብ ግብዓቶቻቸውን አስፍተዋል፡፡ እነ ጉንዳን በቆሎ እና በቋንጣ መልክ እጅ የሚያስቆረጥም መብል መሆናቸውንም እየሰማን ነው፡፡ የተባበት መንግስታት ድርጅት እንዳው ከሆነ፣ እንቁራሪትም ሆነ ትላትሎችን መመገብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አማራጭ የሌላቸው መፍትሔዎች መሆናቸውን አሳስቧል፡፡

መጥምቁ ዮሐንስ እንኳን በዘመኑ የበርሃ አንበጣዎችን በመብላት ሰብላችንን የሚበሉትን እንበላቸው ዘንድ ምሳሌ ሆኖ አልፏል፡፡ አንበጣ ከገብስም በላይ ለሰውነት ጠቃሚ ንጥረ ነገሮች አሉት፡፡

በጥንት ጊዜ አንበጣ በአሦራውያንና በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተወዳጅ ምግብ እንደነበረ ታሪክ ዘግቦታል፡፡ አንዳንድ የአረብ ዘላኖችና የመናውያን አይሁዶች አንበጣ ይበላሉ ነበር፡፡ በእስራኤላውያን ዘንድ አንበጣ የድሆች ምግብ ተደርጎ ይታይ ነበር።

አንድ ስለአንበጣ የወጣ ማስረጃ እንደሚለው፤አንበጦች 75 በመቶ የሚያህል ፕሮቲን ስላላቸው አንድ ሰው አንበጦችን ከዱር ማር ጋር ቢበላ የተመጣጠነ ምግብ ያገኛል።በነገራችን ላይ አንበጣ ለመብልነት ለማዋል ቀላል ነው፡፡ ታዲያ ዛሬ ለምን አንበላውም?! አሰራሩን ለማታውቁ እነሆ በረከት፡-

በመጀመሪያ የአንበጣው ራስ፣ እግሩና ሆዱ ከተወገዱ በኋላ ቀሪው ክፍል ይኸውም ደረቱ ጥሬውን አሊያም ተቆልቶ ወይም በፀሐይ ደርቆ ሊበላ ይችላል፡፡ አንበጣ፣ በጨው ታሽቶ አሊያም በኮምጣጤ ተዘፍዝፎ ወይም በማር ተለውሶ ለመብልነት ሊውል ይችላል፡፡ (ይህ የሚሆነው ግን ለዲዘርት ነው፡፡ ለራበው ሰው ጥሬውን ቢበላ ይመረጣል፡፡)

መልካም ገበታ!

*Share . *Comment .*Invite Your Friends to Like This Page
[የኄኖክ diary ] https://www.facebook.com/henokspad