2013 ጁን 17, ሰኞ

ማነው…. ‘ምንትስ’? ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን


ማነው…. ‘ምንትስ’?
ያው መቸም እኔም እንደሰው
አንዳንዴ÷ አንዳንዴ ብቻ÷ ሕሊናዬን እውነት ሲያምረው
ሰብሰብ ብዬ እማስበው
ቀድሞስ ቢሆን ለኔ ብጤ÷ ለኔ ብጤ የሔዋን ዘር
አዳሜ በኔ ላይ በቀር÷ ለኔ መስክሮ አይናገር”
ብዬ ከልቤ ስማከር
እኔው ከኔው ስከራከር
ተጨብጨ እማብላላው
ያው መቸም እኔም እንደሰው
የሐቅ ራብ ነፍሴን ሲያከው
ልቤ ልቤን ሲሞግተው….
እውነትስ ምንትስ ማነው?”
እያለ ነው፡፡ …..