2013 ጁን 7, ዓርብ

እግር ኳስና ልጅነት



የኳስ ፍቅር አጠርነቴን የተረዳው ጓዴ ባንድ ወቅት እንዲህ ብሎኝ ነበር፡-
ልጅ ሳለህ አንግል ነበርክ እንዴ?”

አዎ! ልጅ ሳለን እንደዛሬው የመጫወቻ ሜዳ በሊዝ ሳይቸበቸብ በፊት፣ እንደዛሬው ኪስ ቦታዎች ለእነ እንቶኔ በማህበር ሳይመሩበት በፊት፣ የላስቲክ እና የካልሲ ኳስ ብርቅ በነበረበት የልጅነት እድሜያችን፣ እኛ ታናናሾች ለታላቆቻችን የእግር ኳስ ጨዋታ የግብ አንግል እንሆን ነበር፡፡ አሁን ሳስበውካፖርተኒ” /የቆዳ ኳስ/ በሽ ሆኖ፣ እንኳን ሊጫወቱበት አንግል ለመሆን ያልታደሉ የእድሜ ታናሾቻችን እድል አሳዘነኝ፡፡

ኄኖክ ስጦታው- henoksitotaw.blogspot.com