2012 ኦክቶበር 9, ማክሰኞ

ለፈጠራት ፀፀት / የትዕግስት ዓለምነህ ግጥም


ለፈጠራት ፀፀት
በሚርመሰመሰው፣ የጥምቀት ታዳሚ፤
የሻሞ እንደሚሏት፣ እንደጣሏት ሎሚ፤
እንደመያዝ ያህል፣ እድል ለሷ ጠባ፣
አይታ ትቀራለች፣ እምነትና ተድላ፤
አለም ግሳንግሷን፣ በእሷው ላይ ቆልላ፡፡
ፍቅሯ እንደ ትልቅ ወንዝ፣ ቢሆንም ፍጥረቷ፤
ገባሮቿ አቅመ ቢስ፣ ሆነው ለህይወቷ፤
መች ሲሻገር አየች፣ ኩራቱ ከመኸር፤
በጋው ሲያብት ጠፋ፣ እንኳን ሊገማሸር፡፡