2012 ዲሴምበር 30, እሑድ

“ትጠምቂልኝ ጀመር”



“ትጠምቂልኝ ጀመር”
ለጠላሽ መጥመቂያ፣ ጋኑን አጥነሻል
ብቅል አብቅለሻል፣ አሻሮ ቆልተሸል
ጌሾ ቀንጥሰሻል፣ እንኩሮ አንኩረሻል…
* * *
ተጠጥቶ ሳያልቅ፣ ከጋን ያለው ጠላ
ቅራሪው ሳይወጣ፣ ትጠምቂያለሽ ሌላ፡፡
* * *
ያን ሰሞን ሳልጠጣ
በፍቅርሽ ሰክሬ፣ ስምሽን ክንዴ ላይ-
በመርፌ ስነቀስ
በምናብ ስቃትት፣ በቅናት ስጠበስ
አንቺም አትጠምቂ፣ እኔም ጠላ አልቀምስ፡፡
የፍቅራችን እድሜ፣ በጨመረ ቁጥር
የጎሸ - ያልጎሸ፣ አንዳንዴም ፍሊተር
ጠላ በየአይነቱ፣ ትጠምቂልኝ ጀመር፡፡
ሄኖክ ስጦታው
 

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ